0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMቲም ዋልዝ ለምክትል ፕሬዝደንትነት እጩ ተወዳዳሪ ሆነው መመረጣቸውን በይፋ ተቀበሉየሜንሶታው አገረ ገዥ ቲም ዋልዝ ለምክትል ፕሬዝደንትነት እንዲወዳደሩ በፓርቲያቸው መመረጣቸውን ትላንት ለሶስተኛ ምሽት በተከናወነው የዲሞክራቲክ ፓርቲው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በይፋ ተቀብለዋል። የቪኦኤው ኬን ፋርቦ ከቺካጎ የላከውን ዘገባ ከተያያዘው ዘገባ ይከታተሉ፡፡0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየፍልስጤም ደጋፊ ተቃዋሚዎች በዲሞክራቲክ ፓርቲ ጉባዔ ላይ ተቃውሞ ማሰማታቸውን ቀጥለዋልበዩናይትድ ስቴትስ፣ የዲሞክራቲክ ፓርቲ ብሔራዊ ጉባኤ በሚካሄድባት ቺካጎ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ የፍልስጤማዊያን ደጋፊዎች የተቃውሞ ሰልፍ ማካሄዳቸውን ቀጥለዋል። ትላንት ረቡዕ በጉባዔው ማዕከል አቅራቢያ የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በአብዛኛው ሰላማዊ ሆኖ ያለፈ ሲሆን፣ ማክሰኞ በእስራኤል ቆንፅላ ፅህፈት ቤት ፊት በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ግን፣ በፖሊስ እና በሰልፈኞች መካከል ግጭት ተቀስቅሶ 56 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበደሴ ከተማ እና በተሁለደሬ ወረዳ የመሬት መንሸራተት አደጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀላቸው ተገለጸበደሴ ከተማ እና በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ በደረሰ የመሬት መንሸራተትና መስረግ አደጋ፣ከ400 በላይ ሰዎች ከቤታቸው ተፈናቅለው በጊዜያዊ መጠለያ መስፈራቸውን፣ የሁለቱም አካባቢዎች አመራሮች አስታወቁ። የደሴ ከተማ የከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ፣ በአደጋው ቤታቸው የፈረሰባቸውንና ለአደጋው ተጋላጭ ይኾናሉ ተብለው የተለዩ ሰዎችን፣ በደረቅ ወይራ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሰፍሩ ማድረጉን ገልጿል፡፡ በተመሳሳይ፣ በተሁለደሬ ወረዳ ቆርኬ በተባለ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMሶማሊያ ‘ሉዓላዊነቴን ይጥሳል’ በሚል የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአየር ክልሏ እንዲበር እንደማትፈቅድ አስጠነቀቀችየሶማሊያ መንግስት “የሉዓላዊነት ጥሰት” ስጋት ነው ያለውን ከበረራ መዳረሻ ጋር የተዛመደ ጉዳይ እስካልተፈታ ድረስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሶማሊያ የሚያደርገውን በረራ ሊያስቆም እንደሚችል አስጠንቅቋል። የሶማሊያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በሰጠው መግለጫ ከዚህ ቀደም ብሎ፣ እንደ አውሮፓውያን የቀን አቆጣጠር ከነሐሴ 14 አንስቶ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የደብዳቤ ልውውጥ ማድረጉን አመልክቷል፡፡0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየዘንድሮው የአሸንዳ በዓል፣በመቐለ ከተማ በድምቀት መከበር ጀምሯልየበዓሉ ተሳታፊዎችም፣በሕወሃት በአመራሮች መካከል የተፈጠረው ፖለቲካዊ ልዩነት በበዓሉ ድምቀት ላይ ተፅእኖ አላሳደረም ሲሉ ተናግረዋል ። ለሁለት የተከፈሉት የህወሓት አመራሮች ተወካዮች ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ መድረክ ላይ በተገኙበት በዐሉ መከበር ጀምሯል፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMካመላ ሄሪስ በፓርቲያቸው ጉባኤ ላይ ንግግር እንደሚያደርጉ በመጠበቅ ላይ ነውየዲሞክራቲክ ፓርቲው ብሔራዊ ጉባኤ ዛሬ ምሽት ሲጠናቀቅ፣ ፓርቲውን ወክለው ለአሜሪካ ፕሬዝደንትነት የሚወዳደሩት ምክትል ፕሬዝደንት ካመላ ሄሪስ ንግግር ያደርጋሉ። ካመላ ሄሪስ ፓርቲያቸው ለፕሬዝደንትነት እንዲወዳደሩ መምረጡንም በይፋ መቀበላቸውን ያሳውቃሉ ተብሎ ይጠበቃል። የአሜሪካ ድምፅ የጉባኤውን የቀጥታ ሂደት እየተከተለ በመድረኩ ላይ የሚደረጉ የንግግሮችን አንኳር ነጥቦች በማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮቹና በድህረ ገፁ ያጋራል።0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMካመላ ሄሪስ ለአሜሪካ ፕሬዝደንትነት በፓርቲው መታጫተቸውን በይፋ ተቀበሉየአሜሪካው ምክትል ፕሬዝደንት ካመላ ሄሪስ ለአሜሪካ ፕሬዝደንትነት እንዲወዳደሩ በፓርቲው መታጫተቸውን በይፋ ተቀበለዋል። ካመላ ሄሪስ እጩ መሆናቸውን በይፋ የተቀበሉት በቺካጎ ከተማ ለአራት ቀናት ሲደረግ በነበረው የፓርቲያቸው ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ ሐሙስ ምሽት ባሰሙት ንግግር ነው። ስለ አስተዳደጋቸውና ስለ ወላጆቻቸው የተናገሩት ካመላ ሄሪስ፣ አስተዳደጋቸው አሁን ያሉበት ቦታ ለመድረሳቸው መሠረት እንደሆነ አስታውቀዋል። ቤተሰብና እምነት ሰዎችን ለመቅረጽ ሚና...0 Comments 0 Shares