0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMበአሰቃቂ ሁኔታ ለተገደለችው ሄቨን ፍትህ ለመጠየቅ የሚደረጉ ጥረቶች ቀጥለዋልበአሰቃዊ ሁኔታ ተደፍራ ለተገደለችው ህጻን ሄቨን አወት የተለያዩ አካላት ፍትህ መጠየቃቸውን የቀጠሉ ሲሆን አርብ እለት አዲስ አበባ በሚገኘው ኢሊሌ ሆቴል ሊደረግ የነበረው እና በጸጥታ አካላት እንዲቋረጥ የተደረገውን ጋዜጣዊ መግለጫ እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር በድጋሚ ለማካሄድ ጥረት እየተደረገ ነው። የእናቶች ወግ ስለልጆች አስተዳደግ እና አመጋገብ የተሰኘው እና በፌስቡክ ላይ ከግማሽ ሚሊየን በላይ አባላት ያሉት ቡድን ቅዳሜ እለት ባካሄደው የደም ልገሳ ፕሮግራም...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMመንግሥት 50 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ እያስገባ መሆኑን አስታወቀመንግሥት የኑሮ ውድነትን የማሻሻል እርምጃ አካል በማድረግ 50 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ አያስገባ መሆኑን አስታውቋል አስተያየታቸውን የሰጡን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ መንግሥት እርምጃ መውሰድ ከጀመረ በኋላ በዘይት ላይ የተወሰነ የዋጋ መሻሻል መኖሩን ገልጸው፣ ኾኖም የዋጋ ንረቱ ፈታኝ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡ የምጣኔ ኃብት ተንታኝ የኾኑት አቶ አማንይሁን ረዳ፣ በሀገር ውስጥ በበቂ መጠን ማምረት እስኪቻል ድረስ፣ የኑሮ ውድነት ጫናን...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMቱኒዚያ ህገወጥ የፍልስተኞች ጀልባ ሠርቷል ያለችውን ጣሊያናዊ ያዘችየቱኒዚያ ባለሥልጣናት ወደ አውሮፓ ለመግባት የሚሞክሩ ህገወጥ ፍልሰተኞች የሚጠቀሙበትን ጀልባ በመስራት የተጠረጠረውን የ45 ዓመቱን ጣሊያናዊ በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ዛሬ ረቡዕ አስታወቁ፡፡ ግለሰቡ በጀልባ ግንባታ ፋብሪካ ውስጥ የሚሠራ መሆኑን በምስራቅ ቱኒዝያ የምትገኘው የሞናስቲር ከተማ አቃቤ ህግ ቃል አቀባይ ፋሪድ ጃሃ ተናግረዋል። ከሜዲትሬኒያን ባህር ወደ አውሮፓ እንዲያሻግር ከፕላስቲክ የተሰራውን ጀልባ ግንባታ በማቀድ የተሳተፉ ሶስት ቱኒዚያውያንም...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበአፍሪካ ለኤምፖክስ የተጋለጡ ወደ 4ሺ ሰዎች ተመዘገቡየአፍሪካ የበሽታ መከላከልና ቁጥጥር ማዕከል ባለፈው ሳምንት በአህጉሪቱ ወደ 4,000 የሚጠጉ ለኤምፖክስ የተጋለጡ አዳዲስ ሰዎች መመዝገባቸውና ወረረሽኙ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን አስታወቀ፡፡ ማዕከሉ በወረረሽኙ እጅግ ወደተጎዳችው ኮንጎ የተላከው የመጀመሪያው ዙር ክትባት በመዘግየቱ አስፈላጊ ክትባቶች በአፋጣኝ እንዲሰጡ በድጋሚ ጥሪውን አቅርቧል፡፡ በአፍሪካ ባለፈው ሳምንት ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ 81 ሰዎች ሞተዋል፡፡ ይህ ቀደም ሲል የነበረውን የሟቾች ቁጥር...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMጄክ ሰለቨን ለባይደንና ሺ ስብሰባ ቻይና ናቸውየዩናይትድ ስቴትስ ብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ጄክ ሰለቨን በህዳር ወር ከሚካሄደው የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በፊት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን አለመግባባት ለማስከን ትላንት ማክሰኞ ከቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ጋር በቤጂንግ ተገናኝተው ተወያይተዋል። ጉብኝቱ ፕሬዝዳንት ባይደን በጥር ወር ስልጣን ከመልቀቃቸው በፊት በፕሬዚዳንት ጆ ባይደን እና በቻይና ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ መካከል ለሚደረገው የመጨረሻ የመሪዎች ጉባኤ መንገድ ለመክፈት ያለመ ነው።...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበእስራኤል የዌስት ባንክ ጥቃት ቢያንስ 9 ሰዎች ተገደሉእስራኤል በዌስት ባንክ ባካሄደችው ጥቃት ቢያንስ ዘጠኝ ፍልስጤማውያን መገደላቸውን የአካባቢው የጤና ባለስልጣናት ዛሬ ረቡዕ ገለጹ። ፍልስጤማውያኑ የተገደሉት ዋነኛው ጥቃትና ግጭት በተካሄደባቸው እስራኤል በያዘቻቸው የተለያዩ የጄኒን እና ቱባስ አካባቢዎች ነው፡፡ እስራኤል ሃማስ እና እስላማዊ ጂሃድን ጨምሮ በኢራን በሚደገፉ የሂዝቦላ ታጣቂ ቡድኖች ላይ የምታካሂደው ወታደራዊ ዘመቻ ጨምሯል፡፡ እኤአ ከጥቅምት 2023 ጀምሮ በዌስት ባንክ ከ640 በላይ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየዳላስ ኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ የነጻ ክሊኒክን እያቋቋመ ነው40ኛ ዓመቱን በዳላስ ያከብራል በዩናይትድ ስቴትሷ የቴክሳስ ክፍለ ግዛት ዳላስ ከተማ የኢትዮጵያውያን ህብረተሰብ ማዕከል ለማህበረሰቡ የነጻ ህክምና አገልግሎት የሚሰጥ ክሊኒክ እያቋቋመ መሆኑን፣ ለዚህም ከግዛቱ የሕክምና አገልግሎት ተቆጣጣሪ ቦርድ እና ለሕብረተሰብ አገልግሎቶች ፈቃድ የሚሰጠውን የግዛቲቱ አስተዳደር ጽ/ቤት ይሁንታ ማግኘቱን አስታውቋል፡፡ የህብረተሰብ ማዕከሉ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አዲስ ጥበቡ ለአሜሪካ ድምጽ እንደተናገሩት ማዕከሉ በቅርቡ የጤና...0 Comments 0 Shares