አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 245 የህክምና ባለሙያዎችን ዛሬ አስመርቋል።

ኮሌጁ ከሚያስመርቃቸው የህክምና ባለሙያዎች ውሰጥ 200 በህክምና ዶክትሬት፣ 23 በጥርስ ህክምና የሰለጠኑ ናቸው።

ለመጀመሪያ ጊዜ በዶክትሬት ዲግሪ የሰለጠኑ 17 የፌዚዮሎጂ እና 5 የካንሰር ስፔሻሊስቶችም እንደተመረቁ ነው የኮሌጁ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ዳዊት ወንድማገኝ የተናገሩት።

በሀገሪቱ የሰለጠነ ባለሙያ እጥረት ባለበት የካንሰር ህክምና ላይ ለምርቃት የሚበቁት የካንሰር ስፔሻሊስቶችም፥ መንግስት የጀመረው የካንሰር ህክምናን በክልሎች የማዳረስ ስራ አጋዥ መሆናቸውን ዶክተር ዳዊት አንስተዋል።

በአሁኑ ወቅትም 30 የካንሰር ስፔሻሊስቶች በስልጠና ላይ የሚገኙ ሲሆን፥ በየዓመቱም 6 ስፔሻሊስቶችን በማስመረቅ በዘርፉ ያለውን የባለሙያ እጥረት ለመቅረፍ ኮሌጁ እየሰራ መሆኑ ተገልጿል።

በተመሳሳይ በአርባ ምንጭ እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች 83 የህክምና ዶክተሮችን ጨምሮ 2 ሺህ 690 ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቀዋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 245 የህክምና ባለሙያዎችን ዛሬ አስመርቋል። ኮሌጁ ከሚያስመርቃቸው የህክምና ባለሙያዎች ውሰጥ 200 በህክምና ዶክትሬት፣ 23 በጥርስ ህክምና የሰለጠኑ ናቸው። ለመጀመሪያ ጊዜ በዶክትሬት ዲግሪ የሰለጠኑ 17 የፌዚዮሎጂ እና 5 የካንሰር ስፔሻሊስቶችም እንደተመረቁ ነው የኮሌጁ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ዳዊት ወንድማገኝ የተናገሩት። በሀገሪቱ የሰለጠነ ባለሙያ እጥረት ባለበት የካንሰር ህክምና ላይ ለምርቃት የሚበቁት የካንሰር ስፔሻሊስቶችም፥ መንግስት የጀመረው የካንሰር ህክምናን በክልሎች የማዳረስ ስራ አጋዥ መሆናቸውን ዶክተር ዳዊት አንስተዋል። በአሁኑ ወቅትም 30 የካንሰር ስፔሻሊስቶች በስልጠና ላይ የሚገኙ ሲሆን፥ በየዓመቱም 6 ስፔሻሊስቶችን በማስመረቅ በዘርፉ ያለውን የባለሙያ እጥረት ለመቅረፍ ኮሌጁ እየሰራ መሆኑ ተገልጿል። በተመሳሳይ በአርባ ምንጭ እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች 83 የህክምና ዶክተሮችን ጨምሮ 2 ሺህ 690 ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቀዋል።
Like
1
0 Comments 0 Shares