የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ኃላፊ የኢስተርን ኢንዱስትሪ ዞንን ጎበኙ
በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ኃላፊ ክርስቲን ላጋርድ ዱከም አካባቢ የሚገኘውን የኢስተርን ኢንዱስትሪ ዞንን ዛሬ ጎብኝተዋል።

በቻይና ባለሃብቶች የተገነባው የኢንዱስትሪ ዞኑ በአጠቃላይ 82 ፋብሪካዎችን የሚይዝ ሲሆን፥ አሁን ላይ 42 ያህሉ ስራ ጀምረዋል።

ክርስቲን ላጋርድ በቦታው ተገኝተው የቻይና እና የኔዘርላንድ ኩባንያዎች ምርት መጀመራቸውን ተመልክተዋል።

ፋብሪካዎቹ የሚያመርቷቸው ምርቶች ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት ጉልህ ሚና ይኖራቸዋል ብለዋል።

የኢንዱስትሪ ዞኑ መገንባትም የአካባቢ ወጣቶች የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል ነው ያሉት።

የአይ ኤም ኤፍ ኃላፊዋ ኢትዮጵያ በርካታ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየገነባች መሆኗን በወሬ ከመስማት ባለፈ በአካል ተገኝቼ በመመልከቴ ደስተኛ ነኝ ብለዋል።

ኢትዮጵያ ያስመዘገበችውን ኢኮኖሚያዊ እድገት ዘላቂ ለማድረግ የግሉ ዘርፍ ሚና ወሳኝ በመሆኑ ይህን ማበረታታት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በአንድ አካል ተሳትፎ የሀገርን እድገት ማስቀጠል አይቻልም ያሉት ኃላፊዋ፥ የመንግስት እና የግል ባለሀብቶች ጥምረት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም መንግስት መሰረተ ልማቶችን ከማሟላት ጀምሮ ሌሎችንም ድጋፎች እንዲያደርግ ነው የገለፁት።

የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ኮሚሽነር አቶ ፍፁም አረጋ በበኩላቸው፥ በሀገሪቱ በግል ባለሃብቶች የሚገነቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች መኖራቸውን ለኃላፊዋ አብራርተውላታል።

መንግስትም የግሉን ዘርፍ ለማበረታታት በርካታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ነው አቶ ፍፁም የተናገሩት።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ኃላፊ የኢስተርን ኢንዱስትሪ ዞንን ጎበኙ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ኃላፊ ክርስቲን ላጋርድ ዱከም አካባቢ የሚገኘውን የኢስተርን ኢንዱስትሪ ዞንን ዛሬ ጎብኝተዋል። በቻይና ባለሃብቶች የተገነባው የኢንዱስትሪ ዞኑ በአጠቃላይ 82 ፋብሪካዎችን የሚይዝ ሲሆን፥ አሁን ላይ 42 ያህሉ ስራ ጀምረዋል። ክርስቲን ላጋርድ በቦታው ተገኝተው የቻይና እና የኔዘርላንድ ኩባንያዎች ምርት መጀመራቸውን ተመልክተዋል። ፋብሪካዎቹ የሚያመርቷቸው ምርቶች ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት ጉልህ ሚና ይኖራቸዋል ብለዋል። የኢንዱስትሪ ዞኑ መገንባትም የአካባቢ ወጣቶች የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል ነው ያሉት። የአይ ኤም ኤፍ ኃላፊዋ ኢትዮጵያ በርካታ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየገነባች መሆኗን በወሬ ከመስማት ባለፈ በአካል ተገኝቼ በመመልከቴ ደስተኛ ነኝ ብለዋል። ኢትዮጵያ ያስመዘገበችውን ኢኮኖሚያዊ እድገት ዘላቂ ለማድረግ የግሉ ዘርፍ ሚና ወሳኝ በመሆኑ ይህን ማበረታታት እንደሚገባ ጠቁመዋል። በአንድ አካል ተሳትፎ የሀገርን እድገት ማስቀጠል አይቻልም ያሉት ኃላፊዋ፥ የመንግስት እና የግል ባለሀብቶች ጥምረት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም መንግስት መሰረተ ልማቶችን ከማሟላት ጀምሮ ሌሎችንም ድጋፎች እንዲያደርግ ነው የገለፁት። የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ኮሚሽነር አቶ ፍፁም አረጋ በበኩላቸው፥ በሀገሪቱ በግል ባለሃብቶች የሚገነቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች መኖራቸውን ለኃላፊዋ አብራርተውላታል። መንግስትም የግሉን ዘርፍ ለማበረታታት በርካታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ነው አቶ ፍፁም የተናገሩት።
Like
2
0 Comments 0 Shares