ልክ የዛሬ 21 ዓመት ይህ ሆኗል
በደቡብ ምስራቅ አፍሪካ የምትገኘው የኮሞሮስ ደሴት ተመራጭ የጎብኚዎች መዳረሻ ስፍራ ነች።
በህንድ ውቅያኖስ ዳርቻ ሲዝናኑ የነበሩ ጎብኚዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ህዳር 14/1989 ዓ.ም ግን ያልተጠበቀ ነገር ተመለከቱ።
ይህንን አሳዛኝ አጋጣሚም በካሜራቸው ቀርጸው ማቆየት የቻሉም ነበሩ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ET961 ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ 175 መንገደኞችን አሳፍሮ በመጓዝ ላይ ሳለ ሶስት ኢትዮጵያን ወደ አውሮፕላኑን መቆጣጠሪያ ክፍል(cockpit) በኃይል በመግባት አብራሪዎቹ የበረራ አቅጣጫቸውን ወደ አውስትራሊያ እንዲያደርጉ አስገደዱ።
አቅጣጫውን እንዲቀይር የተደረገው አውሮፕላን ለአራት...