ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ ስልጣን እንደማይለቁ ገለፁ
በራሳቸው ፍቃድ ከፕሬዚዳንትነታቸው እንዲወርዱ ጫና እየተደረገባቸው ያሉት የዚምባቡዌው ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ ትናንት በሰጡት መግለጫ ስልጣን እንደማይለቁ ተናግረዋል።
በቀጥታ የተሌቪዥን ስርጭት በተላለፈው መግለጫቸው በቀጣይ ታህሳስ ወር በሚደረገው የዛኑ ፒ ኤፍ አጠቃላይ ስበሰባ ላይም ፓርቲያቸውን በመምራት እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ዛኑ ፒኤፍ ፓርቲ ግን በትናነትናው እለት ሮበርት ሙጋቤን ከፓርቲው ሊቀመንበርነት ማንሳቱ ይታወሳል።
ሮበርት ሙጋቤ በ24 ሰዓት ውስጥ ስልጣናቸውን እንዲያስረክቡ፤ ካልሆነ ግን ስልጣናቸው እንደሚነጠቅ ፓርቲው በትናንትናው እለት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
የዚምባቡዌ ጦር ባሳለፍነው ሳምንት...