በሀድያ ሆሳዕና ላይ የተጣለው የ6 ነጥቦች ቅነሳ ተነሳ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሀድያ ሆሳዕና በፌዴሬሽኑ የተጣለበት የስድስት ነጥብ ቅነሳ ቅጣት ተነሳለት።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዲሲፕሊን ኮሚቴ ከሁለት ሳምንት በፊት ባስተላለፈው ውሳኔ፥ የከፍተኛ ሊጉ ክለብ ሀድያ ሆሳዕና ደጋፊዎች በተደጋጋሚ በፈጸሙት የዲሲፕሊን ጥሰት ቡድኑ ከሰበሰበው ነጥብ ላይ ስድስት ነጥቦች እንዲቀነሱበት ውሳኔ ማስተላለፉ የሚታወስ ነው።

ከቅጣት ውሳኔው በኋላ ሀድያ ሆሳዕና ይግባኝ የጠየቀ ሲሆን ጉዳዩን ያየው የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴም ቅጣቱን መሻሩ ታውቋል፡፡

በዚህም ሀድያ ሆሳዕና ከነበረው 30 ነጥብ ላይ የተቀነሰው ስድስት ነጥብ ተጨምሮለት ነጥቡን ወደ 36 በማድረስ ከመሪዎቹ ጅማ ከተማ እና ሀላባ ከተማ ጋር በነጥብ መስተካከል ችሏል።

ሀድያ ሆሳዕና ነጥቡ ቢመለስለትም በምትኩ ሌላ ቅጣት ተጥሎበታል፡፡

በቀጣይ በአቢዮ አርሳሞ ስታዲየም የሚያደርጋቸው ሁለት ጨዋታዎችንም ያለ ደጋፊ በዝግ ስታዲየም እንዲያካሂድ ተወስኖበታል ብሏል የሶከር ኢትዮጵያ ዘገባ።
በሀድያ ሆሳዕና ላይ የተጣለው የ6 ነጥቦች ቅነሳ ተነሳ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሀድያ ሆሳዕና በፌዴሬሽኑ የተጣለበት የስድስት ነጥብ ቅነሳ ቅጣት ተነሳለት። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዲሲፕሊን ኮሚቴ ከሁለት ሳምንት በፊት ባስተላለፈው ውሳኔ፥ የከፍተኛ ሊጉ ክለብ ሀድያ ሆሳዕና ደጋፊዎች በተደጋጋሚ በፈጸሙት የዲሲፕሊን ጥሰት ቡድኑ ከሰበሰበው ነጥብ ላይ ስድስት ነጥቦች እንዲቀነሱበት ውሳኔ ማስተላለፉ የሚታወስ ነው። ከቅጣት ውሳኔው በኋላ ሀድያ ሆሳዕና ይግባኝ የጠየቀ ሲሆን ጉዳዩን ያየው የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴም ቅጣቱን መሻሩ ታውቋል፡፡ በዚህም ሀድያ ሆሳዕና ከነበረው 30 ነጥብ ላይ የተቀነሰው ስድስት ነጥብ ተጨምሮለት ነጥቡን ወደ 36 በማድረስ ከመሪዎቹ ጅማ ከተማ እና ሀላባ ከተማ ጋር በነጥብ መስተካከል ችሏል። ሀድያ ሆሳዕና ነጥቡ ቢመለስለትም በምትኩ ሌላ ቅጣት ተጥሎበታል፡፡ በቀጣይ በአቢዮ አርሳሞ ስታዲየም የሚያደርጋቸው ሁለት ጨዋታዎችንም ያለ ደጋፊ በዝግ ስታዲየም እንዲያካሂድ ተወስኖበታል ብሏል የሶከር ኢትዮጵያ ዘገባ።
0 Comments 0 Shares