ግሬስ ሙጋቤ በአንድ ነጋዴ ላይ ክስ መሠረቱ፡፡
የዚምባቡዌው ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ ባለቤት ግሬስ ሙጋቤ ከ1.35 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ዋጋ ያለው የአልማዝ ቀለበት ለማቅረብ የገባውን ስምምነት ባላከበረው ነጋዴ ላይ ክስ መመስረታቸውን ቢቢሲ ዘገበ ፡፡
ተከሳሹ የሊባኖስ ነጋዴ ጀማል አህመድ ከስምምነታቸው ውጪ የ 30 ሺህ ዶላር ቀለበት በማቅረቡ ንዴት የተሰማቸው ቀዳማዊት እመቤት ትእዛዜ አልተከበረም በሚል ስሜት ጉዳያቸውን ወደ ፍ/ቤት ይዘው ቀርበዋል ፡፡
ከፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ ጋር ጋብቻ የፈጸሙበትን 20ኛ ዓመት ለማክበር ከ100 ካራት በላይ የአልማዝ ቀለበት ለማሰራት ከሊባኖሱ ነጋዴ ጋር ውል የያዙት ግሬስ ሙጋቤ ህግ ይፍረደኝ እያሉ ነው ፡፡
ባለፈው ዓመት የቀዳማዊ እመቤቷ የመጀመሪያ ሴት ልጅ ጋብቻዋን ስትፈጽም ያዘዙት ቀለበት በትክክል አልተሰራም በሚል በዚሁ ነጋዴ ላይ ክስ መስርተው እንደነበር ያብራራው የቢቢሲ ዘጋቢ አሁንም ግለሰቡ ትዕዛዙን አላከበረም በሚል ፍርድ ቤት ሊቀርብ ነው ብሏል፡፡
ክስ የቀረበበት ነጋዴ ግን ሴትየዋ ንብረቴን አልመለሱልኝም ወይም ተገቢውን ክፍያ አልሰጡኝም በሚል ለፍርድ ቤት ክስ በማቅረቡ ምክኒያት ወይዘሮዋ የያዙትን ንብረቶች እንዲመልሱለት የሃገሪቱ ፍርድ ቤት ባለፈው ዓመት ታህሳስ ወር ላይ ትዕዛዝ ማስተላለፉ ይታወሳል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው
ግሬስ ሙጋቤ በአንድ ነጋዴ ላይ ክስ መሠረቱ፡፡
የዚምባቡዌው ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ ባለቤት ግሬስ ሙጋቤ ከ1.35 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ዋጋ ያለው የአልማዝ ቀለበት ለማቅረብ የገባውን ስምምነት ባላከበረው ነጋዴ ላይ ክስ መመስረታቸውን ቢቢሲ ዘገበ ፡፡
ተከሳሹ የሊባኖስ ነጋዴ ጀማል አህመድ ከስምምነታቸው ውጪ የ 30 ሺህ ዶላር ቀለበት በማቅረቡ ንዴት የተሰማቸው ቀዳማዊት እመቤት ትእዛዜ አልተከበረም በሚል ስሜት ጉዳያቸውን ወደ ፍ/ቤት ይዘው ቀርበዋል ፡፡
ከፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ ጋር ጋብቻ የፈጸሙበትን 20ኛ ዓመት ለማክበር ከ100 ካራት በላይ የአልማዝ ቀለበት ለማሰራት ከሊባኖሱ ነጋዴ ጋር ውል የያዙት ግሬስ ሙጋቤ ህግ ይፍረደኝ እያሉ ነው ፡፡
ባለፈው ዓመት የቀዳማዊ እመቤቷ የመጀመሪያ ሴት ልጅ ጋብቻዋን ስትፈጽም ያዘዙት ቀለበት በትክክል አልተሰራም በሚል በዚሁ ነጋዴ ላይ ክስ መስርተው እንደነበር ያብራራው የቢቢሲ ዘጋቢ አሁንም ግለሰቡ ትዕዛዙን አላከበረም በሚል ፍርድ ቤት ሊቀርብ ነው ብሏል፡፡
ክስ የቀረበበት ነጋዴ ግን ሴትየዋ ንብረቴን አልመለሱልኝም ወይም ተገቢውን ክፍያ አልሰጡኝም በሚል ለፍርድ ቤት ክስ በማቅረቡ ምክኒያት ወይዘሮዋ የያዙትን ንብረቶች እንዲመልሱለት የሃገሪቱ ፍርድ ቤት ባለፈው ዓመት ታህሳስ ወር ላይ ትዕዛዝ ማስተላለፉ ይታወሳል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው
0 Comments
0 Shares