የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሙሉ ለሙሉ አሰራሩን ከወረቀት ወደ ዲጂታል
ቴክኖሎጂ መቀየሩን አስታወቀ።
አሰራሩ ከዚህ ቀደም በወረቀት ይሰሩ የነበሩ ሥራዎችን በኮምፒታር
በመጠቀምና በኔትወርክ በማያያዝ የተለያዩ የሥራ ሂደቶችን ያለምንም ወረቀት
በዲጂታል ለመሥራት የሚያስችል ነው።
አዲሱ አሰራር በሰራተኞች ላይ ምንም ዓይነት ተፅዕኖ የማያሳድር፣ ቀልጣፋ
አገልግሎት መስጠት የሚያስችልና ወጪ ቆጣቢ ነው ተብሏል።
የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም
እንደገለጹት፤ድርጅቱ የዲጂታል አሰራር ከጀመረ ከ10 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ
ቢሆንም፣ ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር አልተገባም ነበር።
ከዚህ በኋላ ድርጅቱ አጠቃላይ አሰራሮቹን ሙሉ በሙሉ ከወረቀት በፀዳ መልኩ
የዲጂታል ቴክኖሎጂንእንደሚከተል ገልጸዋል።
የአውሮፕላን ጥገና፣ የበረራና የንግድ አገልግሎቶች፣ የፋይናንስ ሥርዓት፣ የሰው
ኃብት አስተዳድር፣ የኦንላይን ትምህርት፣ አመራር ውሳኔዎች፣ እና ሌሎችም
የሥራ ዓይነቶች በአዲሱ አሰራር መሰረት ገቢራዊ ይደረጋል።
አዲሱ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራር አየር መንገዱን በዓለም አቀፍ ደረጃ
ተወዳዳሪ እንዲሆን ከማድረግ ባለፈ፤ ደንበኞች ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት
እንዲያገኙ ያስችላቸዋልም ብለዋል..........
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሙሉ ለሙሉ አሰራሩን ከወረቀት ወደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ መቀየሩን አስታወቀ። አሰራሩ ከዚህ ቀደም በወረቀት ይሰሩ የነበሩ ሥራዎችን በኮምፒታር በመጠቀምና በኔትወርክ በማያያዝ የተለያዩ የሥራ ሂደቶችን ያለምንም ወረቀት በዲጂታል ለመሥራት የሚያስችል ነው። አዲሱ አሰራር በሰራተኞች ላይ ምንም ዓይነት ተፅዕኖ የማያሳድር፣ ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችልና ወጪ ቆጣቢ ነው ተብሏል። የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም እንደገለጹት፤ድርጅቱ የዲጂታል አሰራር ከጀመረ ከ10 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም፣ ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር አልተገባም ነበር። ከዚህ በኋላ ድርጅቱ አጠቃላይ አሰራሮቹን ሙሉ በሙሉ ከወረቀት በፀዳ መልኩ የዲጂታል ቴክኖሎጂንእንደሚከተል ገልጸዋል። የአውሮፕላን ጥገና፣ የበረራና የንግድ አገልግሎቶች፣ የፋይናንስ ሥርዓት፣ የሰው ኃብት አስተዳድር፣ የኦንላይን ትምህርት፣ አመራር ውሳኔዎች፣ እና ሌሎችም የሥራ ዓይነቶች በአዲሱ አሰራር መሰረት ገቢራዊ ይደረጋል። አዲሱ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራር አየር መንገዱን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ከማድረግ ባለፈ፤ ደንበኞች ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋልም ብለዋል..........
0 Comments 0 Shares