WWW.ETHIOPIANREPORTER.COM
አዲስ አገር በቀል የነዳጅ ኩባንያ ገበያውን ተቀላቀለ
 ጎመጁ ኦይል አትዮጵያ የተሰኘ አዲስ አገር በቀል የነዳጅ ኩባንያ ገበያውን እንደተቀላቀለ አስታወቀ፡፡ በነዳጅ፣ ዘይትና ቅባት ማከፋፈል ሥራ የተሰማራው ጎመጁ ኦይል ኢትዮጵያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በሁለት ኢትዮጵያውያን ባለሀብቶች በ10.7 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተመሠረተ ሲሆን፣ ሥራውን የጀመረው 24 የነዳጅ ማደያዎችን በአዲስ አበባና በተለያዩ የክልል ከተሞች በመገንባት ነው፡፡የጎመጁ ኦይል ጠቅላላ አገልግሎት ክፍል ኃላፊ ወ/ሪት ዓለምፀሐይ ሀብተ ማርያም ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ባለሀብቶቹ በፈሳሽ ጭነት ማመላለሻ ዘርፍ ተሰማርተው ሲሠሩ የቆዩ ናቸው፡፡ በአገሪቱ የሚታየውን የነዳጅ ማደያዎች እጥረት ለመቅረፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማድረግ በማሰብ ኩባንያውን አቋቁመዋል ብለዋል፡፡
0 Comments 0 Shares