አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ ቅጥቅጥ አይሱዙ መለስተኛ የህዘብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተገልብጦ 16 ሰዎች ሞቱ።

ተሽከርካሪው ዛሬ በኦሮሚያ ከልል ምዕራብ ሃረርጌ ዞን ጭሮ ከተማ አቅራቢያ ሲደርስ ነው የተገለበጠው።

በወቅቱ 25 ሰዎች መጫን ቢገባውም 40 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ ነበር ተብሏል።

በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በጭሮ እና አዳማ ሆስፒታሎች የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ሲሆን፥ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ ወደ አዲስ አበባ ተልከዋል።

የምዕራብ ሃረርጌ ዞን ፖሊስ ፅህፈት ቤት፥ ተሽከርካሪው ከልክ በላይ መጫኑን ጠቅሶ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን አስታውቋል።

በሳምንቱ በክልሉ በትራፊክ አደጋ ሳቢያ ከ88 በላይ ሰዎች ህይዎት አልፏል።

በክልሉ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለውን የትራፊክ አደጋ ለመቆጣጠር፥ የክልሉ ትራንስፖርት ባለስልጣን ወደ እርምጃ መግባቱን አስታውቋል።

የባለስልጣኑ ሃላፊ አቶ ታከለ ኡማ እንዳሉት፥ ከዚህ ጋር ተያይዞ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው።

የህዝብ ትራንስፖርት በሌሊት እንዳይሰጥ ማድረግ፣ ስምሪቱን በአዲስ መልክ የማደራጀት፣ የትራፊክ አደጋ የሚበዛባቸው 270 አካባቢዎች ላይ ጥናት ማድረግም እየተተገበሩ ያሉ እርምጃዎች ናቸው ብለዋል።

ይህን ለማስፈጸምም ባለስልጣኑ ከትራፊክ ተቆጣጣሪዎች፣ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ፍትህ ቢሮ፣ ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ፣ መንገዶች ባለስልጣን እና ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ በቅንጅት እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ ቅጥቅጥ አይሱዙ መለስተኛ የህዘብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተገልብጦ 16 ሰዎች ሞቱ። ተሽከርካሪው ዛሬ በኦሮሚያ ከልል ምዕራብ ሃረርጌ ዞን ጭሮ ከተማ አቅራቢያ ሲደርስ ነው የተገለበጠው። በወቅቱ 25 ሰዎች መጫን ቢገባውም 40 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ ነበር ተብሏል። በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በጭሮ እና አዳማ ሆስፒታሎች የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ሲሆን፥ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ ወደ አዲስ አበባ ተልከዋል። የምዕራብ ሃረርጌ ዞን ፖሊስ ፅህፈት ቤት፥ ተሽከርካሪው ከልክ በላይ መጫኑን ጠቅሶ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን አስታውቋል። በሳምንቱ በክልሉ በትራፊክ አደጋ ሳቢያ ከ88 በላይ ሰዎች ህይዎት አልፏል። በክልሉ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለውን የትራፊክ አደጋ ለመቆጣጠር፥ የክልሉ ትራንስፖርት ባለስልጣን ወደ እርምጃ መግባቱን አስታውቋል። የባለስልጣኑ ሃላፊ አቶ ታከለ ኡማ እንዳሉት፥ ከዚህ ጋር ተያይዞ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው። የህዝብ ትራንስፖርት በሌሊት እንዳይሰጥ ማድረግ፣ ስምሪቱን በአዲስ መልክ የማደራጀት፣ የትራፊክ አደጋ የሚበዛባቸው 270 አካባቢዎች ላይ ጥናት ማድረግም እየተተገበሩ ያሉ እርምጃዎች ናቸው ብለዋል። ይህን ለማስፈጸምም ባለስልጣኑ ከትራፊክ ተቆጣጣሪዎች፣ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ፍትህ ቢሮ፣ ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ፣ መንገዶች ባለስልጣን እና ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ በቅንጅት እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
WWW.FANABC.COM
FBC - ከጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ የህዘብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተገልብጦ 16 ሰዎች ሞቱ
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ ቅጥቅጥ አይሱዙ መለስተኛ የህዘብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተገልብጦ 16 ሰዎች ሞቱ። ተሽከርካሪው ዛሬ በኦሮሚያ ከልል ምዕራብ ሃረ...
0 Comments 0 Shares