አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ65 አመቱ ኡጋንዳዊ ሙስታፋ ማጋምቦ ሙቶን ከ176 ልጆቹ መካከል የተወሰኑትን መንግስት እንዲደግፍላቸው ጠይቀዋል።
“13 ሚስቶቼንና ለ170 በላይ ልጆቼን መመገብ ቀላል አይደለም፤ ቢያንስ የ30 ልጆቼን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ወጪ መንግስት እንዲሸፍንልኝ ጠይቄያለሁ” ብለዋል በምዕራባዊ ኡጋንዳ ካጋዲ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ሙቶን።
ከ40 በላይ የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪ ልጆች ያሏቸው ሙቶን፥ በአካባቢያቸው የራሳቸውን ትምህርት ቤት ለመገንባት ማቀዳቸውንም ነው ያስታወቁት።
በማካሬሬ፣ ባራራ እና ኪያምቦጎ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚማ 10 ልጆች አሉኝ፤ የአብዛኞቹ ወጪ በግሌ የሚሸፈኑ ናቸው ብለዋል።
አምስት መንትያ ልጆች ያሏቸው ሙቶን፥ ስድስት ሚስቶቻቸው ነፍሰጡር በመሆናቸው የልጆቻቸው ቁጥር በዚህ አመት መጨረሻ 180ን ይሻገራል ተብሏል።
ሙቶን የኪያተረከራ መንደር ሊቀመንበር ሲሆኑ፥ እንደ አውሮፓውያኑ ጥር 1 1952 ተወልደው በ1968 የመጀመሪያ ትዳራቸውን ይዘዋል።
በ16 አመታቸው ወደ ትዳር የገቡት ሙቶን አሁንም ተጨማሪ ሚስቶችን ለማግባት እና ልጆች ለመውለድ ብርታት አለኝ ይላሉ።
አልኮል እና ስኳር አለመውሰዳቸው እንዲሁም ሲጋራ አለማጨሳቸው አሁንም ጠንካራ እንዲሆኑ ማስቻሉንም አንስተዋል።
በንግድ ስራ የሚተዳደሩት አዛውንት የተወሰኑ ሚስቶች በሙላጎ እና ባራራ ሆስፒታል እና በሩዋንዳ የተለያዩ የጤና ተቋማት በአዋላጅነት ይሰራሉ።
“ወጣቷ ባለቤቴ እድሜዋ 25 ነው፤ ትልቋ ደግሞ 50 አመቷ ነው፤ በይፋ ጋብቻ ከመፈፀሜ በፊት ግን 10 ፍቅረኞች ነበሩኝ፤ ሁሉም በተመሳሳይ አመት የያዝኳቸው ፍቅረኞቼ በዚያው አመት ከእኔ ወልደዋል” ነው ያሉት የ65 አመቱ የልጆች ባለፀጋ።
የመጀመሪያ ልጃቸው 49 አመት፤ የመጨረሻዎቹ ደግሞ የ4 አመት መንትያዎች መሆናቸውንም ነው የተናገሩት።
ሙቶን ከ90 በላይ የልጅ ልጅ እንዳላቸውም ጠቁመዋል።
ሙቶን ስለ እያንዳንዱ ልጆቻቸው መረጃ የሚመዘግቡበት ደብተር እንዳላቸው እና ከኡጋንዳ ውጭ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሩዋንዳ እና ቡሩንዲም የአብራካቸው ክፋዮች እንደሚገኙ አብራርተዋል።
የተወሰኑት ሚስቶቻቸው ከመኖሪያ መንደራቸው ራቅ ብለው የሚገኙ መሆናቸው ፈተና እንደሆነባቸውም ይናገራሉ።
“ከተለያዩ ሚስቶቼ በየቀኑ ከ10 በላይ የስልክ ጥሪዎች ይደርሱኛል፤ ነገር ግን የሁሉንም ጥያቄ መመለስ አልችልም፤ በካጋዲ ብቻ ሰባት ሚስቶች አሉኝ” ነው ያሉት ሙቶን።
“ሚስቶቼን በገንዘብ በመደገፍ ረገድ ምንም ችግር የለብኝም፤ ምክንያቱም አብዛኞቹ እየሰሩ ራሳቸውን ይደግፋሉ” ብለዋል ሙቶን።
ከሙቶን ዘጠኝ ልጆችን የወለደችው የ45 አመት መዲና ቲባሲማ፥ አብዛኞቹ ልጆቿ በውትድርና፣ የመንግስት ስራ እና በህክምና ዘርፍ ስለተሰማሩ የገንዘብ ችግር እንደሌለባት ተናግራለች።
የ45 አመቱ የሙቶን ልጅ ሙሃመድ ያሩፉ በበኩሉ፥ የራሱን የንግድ ተቋም የሚያንቀሳቅስ ሲሆን፥ ለተወሰኑት ወንድም እና እህቶቹ የትምህርት ቤት ክፍያ ይከፍላል።
የተወሰኑ ወንድሞቹ መምህራን በመሆናቸውም ከአባቱ ጋር በመሆን ትምህርት ቤት ለማቋቋም ማሰቡን ገልጿል።
በካጋዲ ሆስፒታል የቤተሰብ ምጣኔ ፕሮግራም ባለሙያ የሆኑት ሞሰስ ባሳሊርዋ፥ በርካታ ልጆችን ማፍራት ከጤና ችግሮች ባሻገር የልጆቹን መሰረታዊ ፍላጎቶች ለማሟላት እና ለማስተማር ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ በመሆኑ በርካታ እክሎችን እንደሚያመጣ ተናግረዋል።
ምንጭ፦ www.newvision.co.ug/
“13 ሚስቶቼንና ለ170 በላይ ልጆቼን መመገብ ቀላል አይደለም፤ ቢያንስ የ30 ልጆቼን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ወጪ መንግስት እንዲሸፍንልኝ ጠይቄያለሁ” ብለዋል በምዕራባዊ ኡጋንዳ ካጋዲ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ሙቶን።
ከ40 በላይ የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪ ልጆች ያሏቸው ሙቶን፥ በአካባቢያቸው የራሳቸውን ትምህርት ቤት ለመገንባት ማቀዳቸውንም ነው ያስታወቁት።
በማካሬሬ፣ ባራራ እና ኪያምቦጎ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚማ 10 ልጆች አሉኝ፤ የአብዛኞቹ ወጪ በግሌ የሚሸፈኑ ናቸው ብለዋል።
አምስት መንትያ ልጆች ያሏቸው ሙቶን፥ ስድስት ሚስቶቻቸው ነፍሰጡር በመሆናቸው የልጆቻቸው ቁጥር በዚህ አመት መጨረሻ 180ን ይሻገራል ተብሏል።
ሙቶን የኪያተረከራ መንደር ሊቀመንበር ሲሆኑ፥ እንደ አውሮፓውያኑ ጥር 1 1952 ተወልደው በ1968 የመጀመሪያ ትዳራቸውን ይዘዋል።
በ16 አመታቸው ወደ ትዳር የገቡት ሙቶን አሁንም ተጨማሪ ሚስቶችን ለማግባት እና ልጆች ለመውለድ ብርታት አለኝ ይላሉ።
አልኮል እና ስኳር አለመውሰዳቸው እንዲሁም ሲጋራ አለማጨሳቸው አሁንም ጠንካራ እንዲሆኑ ማስቻሉንም አንስተዋል።
በንግድ ስራ የሚተዳደሩት አዛውንት የተወሰኑ ሚስቶች በሙላጎ እና ባራራ ሆስፒታል እና በሩዋንዳ የተለያዩ የጤና ተቋማት በአዋላጅነት ይሰራሉ።
“ወጣቷ ባለቤቴ እድሜዋ 25 ነው፤ ትልቋ ደግሞ 50 አመቷ ነው፤ በይፋ ጋብቻ ከመፈፀሜ በፊት ግን 10 ፍቅረኞች ነበሩኝ፤ ሁሉም በተመሳሳይ አመት የያዝኳቸው ፍቅረኞቼ በዚያው አመት ከእኔ ወልደዋል” ነው ያሉት የ65 አመቱ የልጆች ባለፀጋ።
የመጀመሪያ ልጃቸው 49 አመት፤ የመጨረሻዎቹ ደግሞ የ4 አመት መንትያዎች መሆናቸውንም ነው የተናገሩት።
ሙቶን ከ90 በላይ የልጅ ልጅ እንዳላቸውም ጠቁመዋል።
ሙቶን ስለ እያንዳንዱ ልጆቻቸው መረጃ የሚመዘግቡበት ደብተር እንዳላቸው እና ከኡጋንዳ ውጭ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሩዋንዳ እና ቡሩንዲም የአብራካቸው ክፋዮች እንደሚገኙ አብራርተዋል።
የተወሰኑት ሚስቶቻቸው ከመኖሪያ መንደራቸው ራቅ ብለው የሚገኙ መሆናቸው ፈተና እንደሆነባቸውም ይናገራሉ።
“ከተለያዩ ሚስቶቼ በየቀኑ ከ10 በላይ የስልክ ጥሪዎች ይደርሱኛል፤ ነገር ግን የሁሉንም ጥያቄ መመለስ አልችልም፤ በካጋዲ ብቻ ሰባት ሚስቶች አሉኝ” ነው ያሉት ሙቶን።
“ሚስቶቼን በገንዘብ በመደገፍ ረገድ ምንም ችግር የለብኝም፤ ምክንያቱም አብዛኞቹ እየሰሩ ራሳቸውን ይደግፋሉ” ብለዋል ሙቶን።
ከሙቶን ዘጠኝ ልጆችን የወለደችው የ45 አመት መዲና ቲባሲማ፥ አብዛኞቹ ልጆቿ በውትድርና፣ የመንግስት ስራ እና በህክምና ዘርፍ ስለተሰማሩ የገንዘብ ችግር እንደሌለባት ተናግራለች።
የ45 አመቱ የሙቶን ልጅ ሙሃመድ ያሩፉ በበኩሉ፥ የራሱን የንግድ ተቋም የሚያንቀሳቅስ ሲሆን፥ ለተወሰኑት ወንድም እና እህቶቹ የትምህርት ቤት ክፍያ ይከፍላል።
የተወሰኑ ወንድሞቹ መምህራን በመሆናቸውም ከአባቱ ጋር በመሆን ትምህርት ቤት ለማቋቋም ማሰቡን ገልጿል።
በካጋዲ ሆስፒታል የቤተሰብ ምጣኔ ፕሮግራም ባለሙያ የሆኑት ሞሰስ ባሳሊርዋ፥ በርካታ ልጆችን ማፍራት ከጤና ችግሮች ባሻገር የልጆቹን መሰረታዊ ፍላጎቶች ለማሟላት እና ለማስተማር ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ በመሆኑ በርካታ እክሎችን እንደሚያመጣ ተናግረዋል።
ምንጭ፦ www.newvision.co.ug/
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ65 አመቱ ኡጋንዳዊ ሙስታፋ ማጋምቦ ሙቶን ከ176 ልጆቹ መካከል የተወሰኑትን መንግስት እንዲደግፍላቸው ጠይቀዋል።
“13 ሚስቶቼንና ለ170 በላይ ልጆቼን መመገብ ቀላል አይደለም፤ ቢያንስ የ30 ልጆቼን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ወጪ መንግስት እንዲሸፍንልኝ ጠይቄያለሁ” ብለዋል በምዕራባዊ ኡጋንዳ ካጋዲ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ሙቶን።
ከ40 በላይ የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪ ልጆች ያሏቸው ሙቶን፥ በአካባቢያቸው የራሳቸውን ትምህርት ቤት ለመገንባት ማቀዳቸውንም ነው ያስታወቁት።
በማካሬሬ፣ ባራራ እና ኪያምቦጎ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚማ 10 ልጆች አሉኝ፤ የአብዛኞቹ ወጪ በግሌ የሚሸፈኑ ናቸው ብለዋል።
አምስት መንትያ ልጆች ያሏቸው ሙቶን፥ ስድስት ሚስቶቻቸው ነፍሰጡር በመሆናቸው የልጆቻቸው ቁጥር በዚህ አመት መጨረሻ 180ን ይሻገራል ተብሏል።
ሙቶን የኪያተረከራ መንደር ሊቀመንበር ሲሆኑ፥ እንደ አውሮፓውያኑ ጥር 1 1952 ተወልደው በ1968 የመጀመሪያ ትዳራቸውን ይዘዋል።
በ16 አመታቸው ወደ ትዳር የገቡት ሙቶን አሁንም ተጨማሪ ሚስቶችን ለማግባት እና ልጆች ለመውለድ ብርታት አለኝ ይላሉ።
አልኮል እና ስኳር አለመውሰዳቸው እንዲሁም ሲጋራ አለማጨሳቸው አሁንም ጠንካራ እንዲሆኑ ማስቻሉንም አንስተዋል።
በንግድ ስራ የሚተዳደሩት አዛውንት የተወሰኑ ሚስቶች በሙላጎ እና ባራራ ሆስፒታል እና በሩዋንዳ የተለያዩ የጤና ተቋማት በአዋላጅነት ይሰራሉ።
“ወጣቷ ባለቤቴ እድሜዋ 25 ነው፤ ትልቋ ደግሞ 50 አመቷ ነው፤ በይፋ ጋብቻ ከመፈፀሜ በፊት ግን 10 ፍቅረኞች ነበሩኝ፤ ሁሉም በተመሳሳይ አመት የያዝኳቸው ፍቅረኞቼ በዚያው አመት ከእኔ ወልደዋል” ነው ያሉት የ65 አመቱ የልጆች ባለፀጋ።
የመጀመሪያ ልጃቸው 49 አመት፤ የመጨረሻዎቹ ደግሞ የ4 አመት መንትያዎች መሆናቸውንም ነው የተናገሩት።
ሙቶን ከ90 በላይ የልጅ ልጅ እንዳላቸውም ጠቁመዋል።
ሙቶን ስለ እያንዳንዱ ልጆቻቸው መረጃ የሚመዘግቡበት ደብተር እንዳላቸው እና ከኡጋንዳ ውጭ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሩዋንዳ እና ቡሩንዲም የአብራካቸው ክፋዮች እንደሚገኙ አብራርተዋል።
የተወሰኑት ሚስቶቻቸው ከመኖሪያ መንደራቸው ራቅ ብለው የሚገኙ መሆናቸው ፈተና እንደሆነባቸውም ይናገራሉ።
“ከተለያዩ ሚስቶቼ በየቀኑ ከ10 በላይ የስልክ ጥሪዎች ይደርሱኛል፤ ነገር ግን የሁሉንም ጥያቄ መመለስ አልችልም፤ በካጋዲ ብቻ ሰባት ሚስቶች አሉኝ” ነው ያሉት ሙቶን።
“ሚስቶቼን በገንዘብ በመደገፍ ረገድ ምንም ችግር የለብኝም፤ ምክንያቱም አብዛኞቹ እየሰሩ ራሳቸውን ይደግፋሉ” ብለዋል ሙቶን።
ከሙቶን ዘጠኝ ልጆችን የወለደችው የ45 አመት መዲና ቲባሲማ፥ አብዛኞቹ ልጆቿ በውትድርና፣ የመንግስት ስራ እና በህክምና ዘርፍ ስለተሰማሩ የገንዘብ ችግር እንደሌለባት ተናግራለች።
የ45 አመቱ የሙቶን ልጅ ሙሃመድ ያሩፉ በበኩሉ፥ የራሱን የንግድ ተቋም የሚያንቀሳቅስ ሲሆን፥ ለተወሰኑት ወንድም እና እህቶቹ የትምህርት ቤት ክፍያ ይከፍላል።
የተወሰኑ ወንድሞቹ መምህራን በመሆናቸውም ከአባቱ ጋር በመሆን ትምህርት ቤት ለማቋቋም ማሰቡን ገልጿል።
በካጋዲ ሆስፒታል የቤተሰብ ምጣኔ ፕሮግራም ባለሙያ የሆኑት ሞሰስ ባሳሊርዋ፥ በርካታ ልጆችን ማፍራት ከጤና ችግሮች ባሻገር የልጆቹን መሰረታዊ ፍላጎቶች ለማሟላት እና ለማስተማር ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ በመሆኑ በርካታ እክሎችን እንደሚያመጣ ተናግረዋል።
ምንጭ፦ www.newvision.co.ug/
0 Comments
0 Shares