አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 19፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ3 ቢሊየን ብር ወጪ ግዙፍ የገበያ ማዕከል በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው።

“ህዳሴ ግራንድ ሞል” በሚል ስያሜ የሚጠራው የገበያ ማዕከል ግንባታው በሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በተቋቋመው ህዳሴ አክሲዮን ማህበር ይከናወናል ነው የተባለው።

ይህ ዘመናዊ የገበያ ማዕከል በ125 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ የሚያርፍ ሲሆን፥ ጠቅላላ የግቢው ስፋት 250 ሺህ ካሬ ሜትር ይሸፍናል።

የህዳሴ ግራንድ ሞል ስራ አስኪያጅ አቶ ደረጀ መኮንን በሰጡት መግለጫ፥ የገበያ ማዕከሉ ከዚህ ቀደም በአፍሪካ ከሚገኙት በስፋቱና በዘመናዊነቱ የላቀ ይሆናል።

ግንባታው የከተማ አስተዳደሩ ለአክሲዮን ማህበሩ ካመቻቻቸው ዘጠኝ ቦታዎች በአንዱ ላይ ይከናወናል።

የገበያ ማዕከሉ በውስጡ 5 ሺህ ሱቆች፣ 2 ዘመናዊ ባለ አራት ኮከብ ሆቴሎች፣ ባንክና ኢንሹራንስ እንዲሁም ካፌና ሬስቶራንቶችን የሚይዝ ነው።

ማዕከሉ በአንድ ጊዜ 8 ሺህ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ የፓርኪንግ አገልግሎት መስጫ፥ እንዲሁም የመኖሪያ አፓርታማዎች እንደሚኖሩትም ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል።

ግንባታው ሲጠናቀቅ ለ35 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል እንደሚፈጥር ለኢዜአ የገለጹት አቶ ደረጀ፥ ነጋዴውና ሸማቹ ግብይታቸውን በአንድ ቦታ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።

ግንባታውን ለማስጀመር ተቋራጮችን በግልጽ ጨረታ ለማወዳደር ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል።

የገበያ ማዕከሉ ግንባታ በሶስት ዓመት ጊዜ ተጠናቆ ስራ እንደሚጀምርም አቶ ደረጀ ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 19፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ3 ቢሊየን ብር ወጪ ግዙፍ የገበያ ማዕከል በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው። “ህዳሴ ግራንድ ሞል” በሚል ስያሜ የሚጠራው የገበያ ማዕከል ግንባታው በሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በተቋቋመው ህዳሴ አክሲዮን ማህበር ይከናወናል ነው የተባለው። ይህ ዘመናዊ የገበያ ማዕከል በ125 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ የሚያርፍ ሲሆን፥ ጠቅላላ የግቢው ስፋት 250 ሺህ ካሬ ሜትር ይሸፍናል። የህዳሴ ግራንድ ሞል ስራ አስኪያጅ አቶ ደረጀ መኮንን በሰጡት መግለጫ፥ የገበያ ማዕከሉ ከዚህ ቀደም በአፍሪካ ከሚገኙት በስፋቱና በዘመናዊነቱ የላቀ ይሆናል። ግንባታው የከተማ አስተዳደሩ ለአክሲዮን ማህበሩ ካመቻቻቸው ዘጠኝ ቦታዎች በአንዱ ላይ ይከናወናል። የገበያ ማዕከሉ በውስጡ 5 ሺህ ሱቆች፣ 2 ዘመናዊ ባለ አራት ኮከብ ሆቴሎች፣ ባንክና ኢንሹራንስ እንዲሁም ካፌና ሬስቶራንቶችን የሚይዝ ነው። ማዕከሉ በአንድ ጊዜ 8 ሺህ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ የፓርኪንግ አገልግሎት መስጫ፥ እንዲሁም የመኖሪያ አፓርታማዎች እንደሚኖሩትም ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል። ግንባታው ሲጠናቀቅ ለ35 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል እንደሚፈጥር ለኢዜአ የገለጹት አቶ ደረጀ፥ ነጋዴውና ሸማቹ ግብይታቸውን በአንድ ቦታ እንዲያከናውኑ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል። ግንባታውን ለማስጀመር ተቋራጮችን በግልጽ ጨረታ ለማወዳደር ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል። የገበያ ማዕከሉ ግንባታ በሶስት ዓመት ጊዜ ተጠናቆ ስራ እንደሚጀምርም አቶ ደረጀ ጠቁመዋል።
WWW.FANABC.COM
FBC - በአዲስ አበባ ግዙፍ የገበያ ማዕከል በ3 ቢሊየን ብር ሊገነባ ነው
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 19፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ3 ቢሊየን ብር ወጪ ግዙፍ የገበያ ማዕከል በአዲስ አበባ ሊገነባ ነው። “ህዳሴ ግራንድ ሞል” በሚል ስያሜ የሚጠራው የገበያ ማዕከል ግንባታው በሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በተቋቋመው ህዳሴ አ...
0 Comments 0 Shares