ትራክተሮችንና የእርሻ መሣሪያዎችን የሚያመርተው የጣሊያኑ ቬሮና ፔር ኩባንያ ከኢትዮጵያዊያን ጋር መሥራት እፈልጋለሁ አለ
ትራክተሮችንና የእርሻ መሣሪያዎችን የሚያመርተው የጣሊያኑ ቬሮና ፔር ኩባንያ ከኢትዮጵያዊያን ጋር መሥራት እፈልጋለሁ አለ፡፡“ኩባንያው በአዲስ አበባ በተለያየ ጊዜ የሚዘጋጁ አውደ ርዕዮችን አብረን እናሰናዳ የሚል ጥያቄ ለአዲሰ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አቅርቧል፤ ሥራው ለኢትዮጵያ የተሻለ ጥቅም ከሰጠ እንቅበለዋለን፤ ካልሆነ ግን ይቀራል ለማለት በጉዳዩ ላይ እየተመከረ ነው” ሲሉ የንግድ ትርዒት ኃላፊው አቶ ጋሻው አባተ ነግረውናል፡፡
ቬሮና ፔር በመጪው ግንቦት 3 በሚጀምረውና ግንቦት 7 በሚጠናቀቀው 10ኛው የግብርና እና ምግብ አለም አቀፍ ኤግዚብሽን ላይ ይካፈላል ተብሏል፡፡በዚህ አውደ ርዕይ ላይ በመሰል ሥራ የተሰማራው የግብፁ ሹማን ኩባንያም ምርትና አገልግሎቱን ይዞ ይመጣል፤ 11 የአልጄሪያ ኩባንያዎችም ተካፋይ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
ከአፍሪካ ውጭ ደግሞ በግብርናና በምግብ ሥራ የተሰማሩ 30 የቻይና ኩባንያዎችም በአውደ ርዕዩ ይታደማሉ፡፡እንዲህ ያሉ አለም አቀፍ አውደ ርዕዮች በመሰል ሥራ ላይ ላሉ ኢትዮጵያዊያን ልምድ በማካፈል ጥቅማቸው የጐላ ነው ያሉት አቶ ጋሻው 30 ኢትዮጵያዊያን ኩባንያዎችም ምርትና አገልግሎታቸውን ይዘው ይታደሙበታል የልምድ ልውውጥም ይካሄድበታል ሲሉ ነግረውናል፡፡
ሸገር
ትራክተሮችንና የእርሻ መሣሪያዎችን የሚያመርተው የጣሊያኑ ቬሮና ፔር ኩባንያ ከኢትዮጵያዊያን ጋር መሥራት እፈልጋለሁ አለ፡፡“ኩባንያው በአዲስ አበባ በተለያየ ጊዜ የሚዘጋጁ አውደ ርዕዮችን አብረን እናሰናዳ የሚል ጥያቄ ለአዲሰ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አቅርቧል፤ ሥራው ለኢትዮጵያ የተሻለ ጥቅም ከሰጠ እንቅበለዋለን፤ ካልሆነ ግን ይቀራል ለማለት በጉዳዩ ላይ እየተመከረ ነው” ሲሉ የንግድ ትርዒት ኃላፊው አቶ ጋሻው አባተ ነግረውናል፡፡
ቬሮና ፔር በመጪው ግንቦት 3 በሚጀምረውና ግንቦት 7 በሚጠናቀቀው 10ኛው የግብርና እና ምግብ አለም አቀፍ ኤግዚብሽን ላይ ይካፈላል ተብሏል፡፡በዚህ አውደ ርዕይ ላይ በመሰል ሥራ የተሰማራው የግብፁ ሹማን ኩባንያም ምርትና አገልግሎቱን ይዞ ይመጣል፤ 11 የአልጄሪያ ኩባንያዎችም ተካፋይ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
ከአፍሪካ ውጭ ደግሞ በግብርናና በምግብ ሥራ የተሰማሩ 30 የቻይና ኩባንያዎችም በአውደ ርዕዩ ይታደማሉ፡፡እንዲህ ያሉ አለም አቀፍ አውደ ርዕዮች በመሰል ሥራ ላይ ላሉ ኢትዮጵያዊያን ልምድ በማካፈል ጥቅማቸው የጐላ ነው ያሉት አቶ ጋሻው 30 ኢትዮጵያዊያን ኩባንያዎችም ምርትና አገልግሎታቸውን ይዘው ይታደሙበታል የልምድ ልውውጥም ይካሄድበታል ሲሉ ነግረውናል፡፡
ሸገር
ትራክተሮችንና የእርሻ መሣሪያዎችን የሚያመርተው የጣሊያኑ ቬሮና ፔር ኩባንያ ከኢትዮጵያዊያን ጋር መሥራት እፈልጋለሁ አለ
ትራክተሮችንና የእርሻ መሣሪያዎችን የሚያመርተው የጣሊያኑ ቬሮና ፔር ኩባንያ ከኢትዮጵያዊያን ጋር መሥራት እፈልጋለሁ አለ፡፡“ኩባንያው በአዲስ አበባ በተለያየ ጊዜ የሚዘጋጁ አውደ ርዕዮችን አብረን እናሰናዳ የሚል ጥያቄ ለአዲሰ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አቅርቧል፤ ሥራው ለኢትዮጵያ የተሻለ ጥቅም ከሰጠ እንቅበለዋለን፤ ካልሆነ ግን ይቀራል ለማለት በጉዳዩ ላይ እየተመከረ ነው” ሲሉ የንግድ ትርዒት ኃላፊው አቶ ጋሻው አባተ ነግረውናል፡፡
ቬሮና ፔር በመጪው ግንቦት 3 በሚጀምረውና ግንቦት 7 በሚጠናቀቀው 10ኛው የግብርና እና ምግብ አለም አቀፍ ኤግዚብሽን ላይ ይካፈላል ተብሏል፡፡በዚህ አውደ ርዕይ ላይ በመሰል ሥራ የተሰማራው የግብፁ ሹማን ኩባንያም ምርትና አገልግሎቱን ይዞ ይመጣል፤ 11 የአልጄሪያ ኩባንያዎችም ተካፋይ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
ከአፍሪካ ውጭ ደግሞ በግብርናና በምግብ ሥራ የተሰማሩ 30 የቻይና ኩባንያዎችም በአውደ ርዕዩ ይታደማሉ፡፡እንዲህ ያሉ አለም አቀፍ አውደ ርዕዮች በመሰል ሥራ ላይ ላሉ ኢትዮጵያዊያን ልምድ በማካፈል ጥቅማቸው የጐላ ነው ያሉት አቶ ጋሻው 30 ኢትዮጵያዊያን ኩባንያዎችም ምርትና አገልግሎታቸውን ይዘው ይታደሙበታል የልምድ ልውውጥም ይካሄድበታል ሲሉ ነግረውናል፡፡
ሸገር
0 Comments
0 Shares