‹‹ራሴን በእንግሊዝና በኢትዮጵያ መሀል ላይ ያለ ድልድይ አድርጌ ነው የምወስደው››
ገጣሚና ጸሐፊ ለምን ሲሳይ
ትውልደ ኢትዮጵያ ብሪታንያዊው ለምን ሲሳይ ዕውቅ ገጣሚና ጸሐፊ ነው፡፡ በተለያዩ ጥበብ ተኮር ተቋማት እየሠራ ይገኛል፡፡ በሳውዝ ባንክ ማዕከል ተባባሪ አርቲስት፣ በሌተር ቦክስ ክለብ ድጋፍ ሰጪ፣ የቺልድረንስ ሪዲንግ ፈንድ አምባሳደር ሲሆን የክብር ዶክትሬት (ዶክተር ኦፍ ሌተርስ) ተሰጥቶታል፡፡ ለለንደን ኦሊምፒክ ግጥም የደረሰ፣ የበርካታ ተለጣጣቂ መጻሕፍት፣ መጣጥፎች፣ ሪከርዶች ወዘተ ጸሐፊ ነው፡፡ ከሰኔ 2007 ዓ.ም. ጀምሮ የማንችስተር ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆኖ ለሰባት ዓመታት አገልግሎት ተመርጧል፡፡ ኢትዮጵያ ተወልዶ ብሪታኒያ በጉዲፈቻ ያደገው ለምን ሕይወቱን ከአፄ ቴዎድሮስ ልጅ ልዑል ዓለማየሁ ጋር ያገናኘዋል፡፡ የልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ አፅም ወደ አገሩ እንዲመለስ ምኞቱ መሆኑንም ይናገራል፡፡ መሰንበቻውን ወደ ኢትዮጵያ ጎራ ያለውን ለምን ሲሳይን ዳዊት እንደሻው ስለ ዐውደ ሕይወቱ አውግቶታል፡፡
ሪፖርተር፡- በቅድሚያ ስለነበረህ የአንድ ሳምንት ቆይታ እስኪ ግለጽልን፡፡
ለምን፡- እስካሁን የነበረኝ ቆይታ በጣም አዝናኝና ፍሬያማ ነበር፡፡ ከብዙ ሰዎች ጋር የመገናኘቱን ዕድል አግኝቻለሁ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ከሪታ ፓንክረስት ጋር የመገናኘቱን ክብር አግኝቻለሁ፡፡ በተጨማሪም አሉላ ፓንክረስት ጋር ተገናኝቼ ከማንችስተር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት እንዴት የውጭ የትምህርት ዕድል ለኢትዮጵያውያን ማመቻቸት እንደምንችል መክረናል፡፡
እሱ ብቻ አይደለም ከብሪትሽ ካውንስል አዲስ ዳይሬክተር ፒተር ብራውን ጋር ተገናኝተናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከአዲስ አበባና ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ከመጡ ምሁራን ጋርም የመገናኘቱን ዕድልም አግኝቼ ከውጭ የትምህርት ዕድሉ ጋር በተያያዘ እንዴት የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ከማንችስተር ዩኒቨርሲቲ ጋር እንዴት መሥራት እንደሚችሉ ተነጋግረናል፡፡ እንግዲህ እኔ ራሴን በእንግሊዝና በኢትዮጵያ መሀል ላይ ያለ ድልድይ አድርጌ ነው የምወስደው፡፡ አሁን አሁን ጊዜዎች ባለፉ ዕድሜያችንም በገፋ ቁጥር እኔ እዚህ ያለሁት ለምክንያት ነው የሚለው ሐሳብ ሁሌም ይመጣብኛል፡፡ ይኼ ደግሞ ለእኔ መባረክ ነው፡፡ በዚች ታላቅ አገር ውስጥ በሚኖሩ ሰዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ ተቀባይነትን ባገኘሁ ቁጥር በታወኩ ቁጥር ለእኔ ይሄ ትልቅ ነገር ነው፤ ስጦታ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ መሆን ከኢትዮጵያ መፈጠር ትልቅ ስጦታ ነው፡፡
ሪፖርተር፡- እስኪ ደግሞ ወደ ልጅነት ታሪክህ እንመለስ ከኢትዮጵያ ቤተሰቦች ተወለድክ፣ ለእንግሊዛዊ ቤተሰቦች ተሰጠህ እንደገና ደግሞ ተላልፈህ የልጆች ማሳደጊያ ማዕከል ወስጥ አደግክ፡፡ እስኪ ይኼ የልጅነት ጊዜህ የአሁኑን ለምን ሲሳይን በምን መንገድ ቀርጿል?
ለምን፡- ከምንም በላይ ብዙ አሉታዊ ነገሮች ቢያልፉም አሁን ያለሁበት ላይ ደርሻለሁ፡፡ ይህ ማለት ግን ለምን በልጅነቱ በብዙ መጥፎ ነገሮች ስላለፈ በዚህም ምክንያት አሁን ያለበት ጥሩ ደረጃ ላይ ደርሷል ማለት አይደለም፡፡ እርግጥ ነው በብዙ መጥፎ ነገሮች ውስጥ አልፌያለሁ ስለዚህ መጠየቅ ያለብኝ በዚህ ውስጥ እኔ ማን ነኝ? የሚለውን ነው በመጥፎ ነገሮች ውስጥ በማለፌ ንዴት ውስጥ ገባሁ፣ ሌሎችን ጎዳሁ ወይስ ራሴን አደጋ ላይ ጣልኩ? በተቃራኒው የእኔ መገፋት፣ ሕመምና ስቃይ የሌሎችን ሕመም እንድረዳ እንዲሁም የመዳንን ኃይል እንድረዳ አድርጎኛል፡፡ እንደ እኔ የመዳን ኃይል ከመሠረቴ ነው ሥር መሠረቴ ደግሞ ከዚሁ ከኢትዮጵያ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች እንግሊዝ ስላደገ፣ ጥሩ ትምህርት ስለተማረ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሷል ይላሉ ነገር ግን ጥሩ ትምህርት አልነበረኝም ነበር፣ ተጎድቼ ነበር፡፡ እኔ እማውቀው ይኼን ሁሉ አሽንፌ መምጣቴን ነው፡፡ ብዙዎቻችን በቤተሰበ፣ በማኅበረሰብ ውስጥ እንዲሁም በተለያዩ ነገሮች ስናልፍ ብዙ መጥፎ ልምዶች ሊኖሩን ይችላሉ፣ ልንጎዳ እንችላለን፡፡ ነገር ግን ጥያቄው የእኛ መጎዳት ሌሎችን እንድንጎዳ መብት ይሰጠናል ወይ? የእኛ መጎዳት ሌሎችን እንድንጎዳ በፍጹም መብት አይሰጠንም፡፡ በተቃራኒው የእኛ መጎዳት የሌሎችን ሕመም፣ መገፋት እንዲሁም መነጠልን እንድንረዳ ያደርገናል፡፡ ይረዳናል፡፡ ይኼን ያህል ካወቅኩ እኔ ላይ የሆነው ሌሎች ላይ እንዲደገም አልፈልግም፡፡ ማነህ አንተ? እንግሊዛዊ ነህ? አይሪሽ ነህ ወይስ ኤርትራዊ ወይስ ደግሞ ሶማሊያዊ … ለእኔ አንተ ማለት ወንድሜ ነህ እዚህ ላይ በመተማመን አብሮ መሥራት፣ መኖር ይቻላል፡፡
ሪፖርተር፡- እስኪ ከወላጅ እናትህ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ስትግናኙ ስለነበረው ነገር ንገረኝ?
ለምን፡- የሚገርም ስሜት ነበር፡፡ የማርሸት ሲሳይ ወላጅ እናቴ በጣም የምትገርምና ጠንካራ ሴት ነች፡፡ እንደ አብዛኛው 1950ዎቹ 60ዎች ትውልድ ለትምህርት ወደ ውጭ የመሄድ ዕድል አግኝታ ነበር፡፡ በዚያ ጊዜ ለትምህርት ወደ ውጭ የሄዱት የእናቴ ዓይነት ወጣቶች በዚያን ጊዜ የነበረውን የኢትዮጵያ መንፈስ ይዘው ዓለምን ዞረዋል፡፡ በጊዜው እናቴ እኔን አረገዘች ከዚያ ለጉዲፈቻ ሰጠችኝ፡፡ ብዙ ሰው የማያውቀው እናቴ ተመልሳ እኔን ለማግኘት ሞክራ እንደነበር ነው፡፡ እኔ ለሕፃናት ማዕከሉ በጻፈችው ደብዳቤ ልጇን እንደምትፈልግ፣ ልጇ በአገሩ እንዲያድግ እንደምትፈልግና በሰው አገር መገለል እንዳይደርስበት ገልጻ ነበር፡፡ በጊዜው እናቴ 21 ዓመቷ ነበር፡፡ እናቴ የሚቻላትን አድርጋ ነበር ግን እንግሊዞቹ መልሰው እኔን ሊሰጧት አልፈለጉም፡፡
ሪፖርተር፡- ለእናትህ አስቸጋሪ ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል?
ለምን፡- በጣም እንጂ ማሰቡ ራሱ ይከብዳል፡፡ ከዚያ እናቴ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰች፣ መመለስም ነበረባት ምክንያቱም በጊዜው አባቷ ታመው ነበር ከዚያም አቶ አሸናፊ ሽፈራውን አገባች፡፡ ከዚያም ከአምስት ዓመት በኋላ ደርግ ሥልጣን ያዘ፣ ባሏ ታሰረ፡፡ ስለዚህ ለሕይወቷ ስትል አገሩን ለቃ መሄድ ነበረባት፡፡ ጠንካራ ሴት ነበረች፡፡ ከብዙ ዓመት በኋላ 21 ዓመት ሲሆነኝ እናቴን አገኘሁ፡፡ ቀላል አልነበረም በእውነቱ፣ በጊዜው እሷን ማግኘት ውብ ነበር፡፡ እሷን ማግኘት ወደ ቤት እንደመመለስ ነበር ወደ ኢትዮጵያ፡፡
ሪፖርተር፡- ኢትዮጵያ ውስጥ ተወልጄ፣ አድጌ ቢሆን ብለህ ታውቃለህ?
ለምን፡- እሱንማ በምን ዕድሌ፡፡ ሁሌም የምፈልገው ነው ግን ደግሞ ማግኘት ያልቻልኩት ነው፡፡ ስለዚህ ያለኝን መቀበልና ባለኝ ነገር መኖር ነው፡፡ እውነቱን ለመቀበል በልጅነቴ የሚያውቁኝ እናት፣ አባት እንዲሁም እህትና ወንድም የለኝመ፡፡ ትልቁን የሕይወት ዘመኔን ሕልምና ምኞት ልንገርህ? የልዑል ዓለማየሁ አፅም ወደ አገሩ ሲመለስ ማየት ለእኔ ትልቅ ነገር ነው፡፡ ሕይወቱ ከእኔ ጋር ይገናኛል ብዬ አስባለሁ፡፡
ሪፖርተር፡- ስለዚህ የእሱ ሕይወት ከአንተ ጋር ይገናኛል ብለህ ታስባለህ ማለት ነው?
ለምን፡- በእንግሊዞች ከአገሩ ተወስዷል፡፡ አሥራ ስምንት ዓመት እስኪሞላው በካፒቴን ስፒዲ ሥር ሆኖ አድጓል፣ ከዚያም ሊድስ ወደ ተባለ ሰሜን ኢንግላንድ ወሰዱት፡፡ ከዚያም በዓመት ውስጥ ሞተ፡፡ እንደሚሉት ሞቱ የተፈጥሮ ሞት ነው ይላሉ፡፡ ለእኔ ይኼ አይዋጥልኝም፡፡ የሆነ ነገር ነበር የሆነ! ብዙ መጠናት ያለባቸው ብዙ የማናውቃቸው ነገሮች አሉ፡፡ እኔ ወደ አገሬ እንደተመለስኩ እሱም እንዲመለስ እፈልጋለሁ፡፡
ሪፖርተር፡- ራስህን ማን ነኝ የምትለው?
ለምን፡- ኢትዮጵያዊ፣ እንግሊዛዊ፣ የዓለም ዜጋ፣ የሞሎኪሎች የመንፈሶች ስብስብ፡፡
ሪፖርተር፡- ስለራስህ ስናነሳ ብዙ ሰዎች በኢትዮጵያ እንግሊዝኛ ማንበብም ሆነ መረዳት አይችሉም ሥራህን ለመተርጎም ያሰብከው ነገር አለ?
ለምን፡- የተወጠኑ ነገሮች አሉ እስካሁን ባይሳኩም፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት ከኤፍሬም ሥዩም ጋር አብረን እየሠራን ነው፡፡ ጥሩ የቋንቋ ችሎታ ያለው የጥበብ ሰው ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ገጣሚዎች ኤፍሬምን እንዲሁም የበውቀቱ ስዩምን ሥራዎች አደንቃለሁ፡፡ ትልቅ የሥነ ግጥም ሀብት ያለበት አገር ነው፡፡
ሪፖርተር፡- ብዙ ጊዜ ስለ መነሳሳት ወይም መነቃቃት ትናገራለህ፡፡ በአንዱም ንግግር የአንተ ዓላማ በሰዎች መነሳት ወይም ደግሞ ሰዎችን ማነሳሳት (Inspire) ማድረግ ነው ብለህ ነበር፡፡ አንተን በጠዋት አንቅቶ ግጥም እንድትጽፍ የሚያደርግህ ምንድን ነው?
ለምን፡- ሁሌም ከእንቅልፌ ስነቃ ግጥሞችን በማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ እለቃለሁ ይኼን ደግሞ እስክሞት የምቀጥለው ነገር ነው፡፡ ….. ፈጠራ ሙሉ በሙሉ በአርቲስቶች ቁጥጥር የተያዘ አይደለም፡፡ ሁሉም ሰው በራሱ መንገድ ፈጣሪ ነው፡፡ ስለዚህ የእኔ ሥራ መነቃቃትን ወይም ሰዎችን ማንቃት መፈለግ ነው፡፡ መማር እና ማስተማር፡፡
ሪፖርተር፡- መቼ ነው ግጥም መጻፍ እንደምትችል ያወቅከው?
ለምን፡- ለምን የሚለው ስሜ መሆኑን ከማወቄ በፊት መግጠም ጀምሬ ነበር፡፡ ለምን የሚለውን ስም ይዤ እንዴት ገጣሚ መሆን አልችልም፡፡ እንግሊዞቹ የሰጡኝን ስም ይዤ እገጥም ነበር፡፡ ስለዚህ ገጣሚ ሆኜ ነው የተወለድኩት ማለት ይቻላል፡፡
ሪፖርተር፡- እስካሁን ያለህ የቻንስለርነት ቆይታ ምንይመስላል?
ለምን፡- ጥሩ ነው፡፡ ለተማሪዎቼ የተስፋ ምንጭ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ፡፡
ሪፖርተር፡- የራስህ ቤተሰብ የመመሥረት ሐሳብ አለህ?
ለምን፡- ምን አልባት ወደ ፊት፡፡
ሪፖርተር
ገጣሚና ጸሐፊ ለምን ሲሳይ
ትውልደ ኢትዮጵያ ብሪታንያዊው ለምን ሲሳይ ዕውቅ ገጣሚና ጸሐፊ ነው፡፡ በተለያዩ ጥበብ ተኮር ተቋማት እየሠራ ይገኛል፡፡ በሳውዝ ባንክ ማዕከል ተባባሪ አርቲስት፣ በሌተር ቦክስ ክለብ ድጋፍ ሰጪ፣ የቺልድረንስ ሪዲንግ ፈንድ አምባሳደር ሲሆን የክብር ዶክትሬት (ዶክተር ኦፍ ሌተርስ) ተሰጥቶታል፡፡ ለለንደን ኦሊምፒክ ግጥም የደረሰ፣ የበርካታ ተለጣጣቂ መጻሕፍት፣ መጣጥፎች፣ ሪከርዶች ወዘተ ጸሐፊ ነው፡፡ ከሰኔ 2007 ዓ.ም. ጀምሮ የማንችስተር ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆኖ ለሰባት ዓመታት አገልግሎት ተመርጧል፡፡ ኢትዮጵያ ተወልዶ ብሪታኒያ በጉዲፈቻ ያደገው ለምን ሕይወቱን ከአፄ ቴዎድሮስ ልጅ ልዑል ዓለማየሁ ጋር ያገናኘዋል፡፡ የልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ አፅም ወደ አገሩ እንዲመለስ ምኞቱ መሆኑንም ይናገራል፡፡ መሰንበቻውን ወደ ኢትዮጵያ ጎራ ያለውን ለምን ሲሳይን ዳዊት እንደሻው ስለ ዐውደ ሕይወቱ አውግቶታል፡፡
ሪፖርተር፡- በቅድሚያ ስለነበረህ የአንድ ሳምንት ቆይታ እስኪ ግለጽልን፡፡
ለምን፡- እስካሁን የነበረኝ ቆይታ በጣም አዝናኝና ፍሬያማ ነበር፡፡ ከብዙ ሰዎች ጋር የመገናኘቱን ዕድል አግኝቻለሁ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ከሪታ ፓንክረስት ጋር የመገናኘቱን ክብር አግኝቻለሁ፡፡ በተጨማሪም አሉላ ፓንክረስት ጋር ተገናኝቼ ከማንችስተር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት እንዴት የውጭ የትምህርት ዕድል ለኢትዮጵያውያን ማመቻቸት እንደምንችል መክረናል፡፡
እሱ ብቻ አይደለም ከብሪትሽ ካውንስል አዲስ ዳይሬክተር ፒተር ብራውን ጋር ተገናኝተናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከአዲስ አበባና ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ከመጡ ምሁራን ጋርም የመገናኘቱን ዕድልም አግኝቼ ከውጭ የትምህርት ዕድሉ ጋር በተያያዘ እንዴት የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ከማንችስተር ዩኒቨርሲቲ ጋር እንዴት መሥራት እንደሚችሉ ተነጋግረናል፡፡ እንግዲህ እኔ ራሴን በእንግሊዝና በኢትዮጵያ መሀል ላይ ያለ ድልድይ አድርጌ ነው የምወስደው፡፡ አሁን አሁን ጊዜዎች ባለፉ ዕድሜያችንም በገፋ ቁጥር እኔ እዚህ ያለሁት ለምክንያት ነው የሚለው ሐሳብ ሁሌም ይመጣብኛል፡፡ ይኼ ደግሞ ለእኔ መባረክ ነው፡፡ በዚች ታላቅ አገር ውስጥ በሚኖሩ ሰዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ ተቀባይነትን ባገኘሁ ቁጥር በታወኩ ቁጥር ለእኔ ይሄ ትልቅ ነገር ነው፤ ስጦታ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ መሆን ከኢትዮጵያ መፈጠር ትልቅ ስጦታ ነው፡፡
ሪፖርተር፡- እስኪ ደግሞ ወደ ልጅነት ታሪክህ እንመለስ ከኢትዮጵያ ቤተሰቦች ተወለድክ፣ ለእንግሊዛዊ ቤተሰቦች ተሰጠህ እንደገና ደግሞ ተላልፈህ የልጆች ማሳደጊያ ማዕከል ወስጥ አደግክ፡፡ እስኪ ይኼ የልጅነት ጊዜህ የአሁኑን ለምን ሲሳይን በምን መንገድ ቀርጿል?
ለምን፡- ከምንም በላይ ብዙ አሉታዊ ነገሮች ቢያልፉም አሁን ያለሁበት ላይ ደርሻለሁ፡፡ ይህ ማለት ግን ለምን በልጅነቱ በብዙ መጥፎ ነገሮች ስላለፈ በዚህም ምክንያት አሁን ያለበት ጥሩ ደረጃ ላይ ደርሷል ማለት አይደለም፡፡ እርግጥ ነው በብዙ መጥፎ ነገሮች ውስጥ አልፌያለሁ ስለዚህ መጠየቅ ያለብኝ በዚህ ውስጥ እኔ ማን ነኝ? የሚለውን ነው በመጥፎ ነገሮች ውስጥ በማለፌ ንዴት ውስጥ ገባሁ፣ ሌሎችን ጎዳሁ ወይስ ራሴን አደጋ ላይ ጣልኩ? በተቃራኒው የእኔ መገፋት፣ ሕመምና ስቃይ የሌሎችን ሕመም እንድረዳ እንዲሁም የመዳንን ኃይል እንድረዳ አድርጎኛል፡፡ እንደ እኔ የመዳን ኃይል ከመሠረቴ ነው ሥር መሠረቴ ደግሞ ከዚሁ ከኢትዮጵያ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች እንግሊዝ ስላደገ፣ ጥሩ ትምህርት ስለተማረ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሷል ይላሉ ነገር ግን ጥሩ ትምህርት አልነበረኝም ነበር፣ ተጎድቼ ነበር፡፡ እኔ እማውቀው ይኼን ሁሉ አሽንፌ መምጣቴን ነው፡፡ ብዙዎቻችን በቤተሰበ፣ በማኅበረሰብ ውስጥ እንዲሁም በተለያዩ ነገሮች ስናልፍ ብዙ መጥፎ ልምዶች ሊኖሩን ይችላሉ፣ ልንጎዳ እንችላለን፡፡ ነገር ግን ጥያቄው የእኛ መጎዳት ሌሎችን እንድንጎዳ መብት ይሰጠናል ወይ? የእኛ መጎዳት ሌሎችን እንድንጎዳ በፍጹም መብት አይሰጠንም፡፡ በተቃራኒው የእኛ መጎዳት የሌሎችን ሕመም፣ መገፋት እንዲሁም መነጠልን እንድንረዳ ያደርገናል፡፡ ይረዳናል፡፡ ይኼን ያህል ካወቅኩ እኔ ላይ የሆነው ሌሎች ላይ እንዲደገም አልፈልግም፡፡ ማነህ አንተ? እንግሊዛዊ ነህ? አይሪሽ ነህ ወይስ ኤርትራዊ ወይስ ደግሞ ሶማሊያዊ … ለእኔ አንተ ማለት ወንድሜ ነህ እዚህ ላይ በመተማመን አብሮ መሥራት፣ መኖር ይቻላል፡፡
ሪፖርተር፡- እስኪ ከወላጅ እናትህ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ስትግናኙ ስለነበረው ነገር ንገረኝ?
ለምን፡- የሚገርም ስሜት ነበር፡፡ የማርሸት ሲሳይ ወላጅ እናቴ በጣም የምትገርምና ጠንካራ ሴት ነች፡፡ እንደ አብዛኛው 1950ዎቹ 60ዎች ትውልድ ለትምህርት ወደ ውጭ የመሄድ ዕድል አግኝታ ነበር፡፡ በዚያ ጊዜ ለትምህርት ወደ ውጭ የሄዱት የእናቴ ዓይነት ወጣቶች በዚያን ጊዜ የነበረውን የኢትዮጵያ መንፈስ ይዘው ዓለምን ዞረዋል፡፡ በጊዜው እናቴ እኔን አረገዘች ከዚያ ለጉዲፈቻ ሰጠችኝ፡፡ ብዙ ሰው የማያውቀው እናቴ ተመልሳ እኔን ለማግኘት ሞክራ እንደነበር ነው፡፡ እኔ ለሕፃናት ማዕከሉ በጻፈችው ደብዳቤ ልጇን እንደምትፈልግ፣ ልጇ በአገሩ እንዲያድግ እንደምትፈልግና በሰው አገር መገለል እንዳይደርስበት ገልጻ ነበር፡፡ በጊዜው እናቴ 21 ዓመቷ ነበር፡፡ እናቴ የሚቻላትን አድርጋ ነበር ግን እንግሊዞቹ መልሰው እኔን ሊሰጧት አልፈለጉም፡፡
ሪፖርተር፡- ለእናትህ አስቸጋሪ ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል?
ለምን፡- በጣም እንጂ ማሰቡ ራሱ ይከብዳል፡፡ ከዚያ እናቴ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰች፣ መመለስም ነበረባት ምክንያቱም በጊዜው አባቷ ታመው ነበር ከዚያም አቶ አሸናፊ ሽፈራውን አገባች፡፡ ከዚያም ከአምስት ዓመት በኋላ ደርግ ሥልጣን ያዘ፣ ባሏ ታሰረ፡፡ ስለዚህ ለሕይወቷ ስትል አገሩን ለቃ መሄድ ነበረባት፡፡ ጠንካራ ሴት ነበረች፡፡ ከብዙ ዓመት በኋላ 21 ዓመት ሲሆነኝ እናቴን አገኘሁ፡፡ ቀላል አልነበረም በእውነቱ፣ በጊዜው እሷን ማግኘት ውብ ነበር፡፡ እሷን ማግኘት ወደ ቤት እንደመመለስ ነበር ወደ ኢትዮጵያ፡፡
ሪፖርተር፡- ኢትዮጵያ ውስጥ ተወልጄ፣ አድጌ ቢሆን ብለህ ታውቃለህ?
ለምን፡- እሱንማ በምን ዕድሌ፡፡ ሁሌም የምፈልገው ነው ግን ደግሞ ማግኘት ያልቻልኩት ነው፡፡ ስለዚህ ያለኝን መቀበልና ባለኝ ነገር መኖር ነው፡፡ እውነቱን ለመቀበል በልጅነቴ የሚያውቁኝ እናት፣ አባት እንዲሁም እህትና ወንድም የለኝመ፡፡ ትልቁን የሕይወት ዘመኔን ሕልምና ምኞት ልንገርህ? የልዑል ዓለማየሁ አፅም ወደ አገሩ ሲመለስ ማየት ለእኔ ትልቅ ነገር ነው፡፡ ሕይወቱ ከእኔ ጋር ይገናኛል ብዬ አስባለሁ፡፡
ሪፖርተር፡- ስለዚህ የእሱ ሕይወት ከአንተ ጋር ይገናኛል ብለህ ታስባለህ ማለት ነው?
ለምን፡- በእንግሊዞች ከአገሩ ተወስዷል፡፡ አሥራ ስምንት ዓመት እስኪሞላው በካፒቴን ስፒዲ ሥር ሆኖ አድጓል፣ ከዚያም ሊድስ ወደ ተባለ ሰሜን ኢንግላንድ ወሰዱት፡፡ ከዚያም በዓመት ውስጥ ሞተ፡፡ እንደሚሉት ሞቱ የተፈጥሮ ሞት ነው ይላሉ፡፡ ለእኔ ይኼ አይዋጥልኝም፡፡ የሆነ ነገር ነበር የሆነ! ብዙ መጠናት ያለባቸው ብዙ የማናውቃቸው ነገሮች አሉ፡፡ እኔ ወደ አገሬ እንደተመለስኩ እሱም እንዲመለስ እፈልጋለሁ፡፡
ሪፖርተር፡- ራስህን ማን ነኝ የምትለው?
ለምን፡- ኢትዮጵያዊ፣ እንግሊዛዊ፣ የዓለም ዜጋ፣ የሞሎኪሎች የመንፈሶች ስብስብ፡፡
ሪፖርተር፡- ስለራስህ ስናነሳ ብዙ ሰዎች በኢትዮጵያ እንግሊዝኛ ማንበብም ሆነ መረዳት አይችሉም ሥራህን ለመተርጎም ያሰብከው ነገር አለ?
ለምን፡- የተወጠኑ ነገሮች አሉ እስካሁን ባይሳኩም፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት ከኤፍሬም ሥዩም ጋር አብረን እየሠራን ነው፡፡ ጥሩ የቋንቋ ችሎታ ያለው የጥበብ ሰው ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ገጣሚዎች ኤፍሬምን እንዲሁም የበውቀቱ ስዩምን ሥራዎች አደንቃለሁ፡፡ ትልቅ የሥነ ግጥም ሀብት ያለበት አገር ነው፡፡
ሪፖርተር፡- ብዙ ጊዜ ስለ መነሳሳት ወይም መነቃቃት ትናገራለህ፡፡ በአንዱም ንግግር የአንተ ዓላማ በሰዎች መነሳት ወይም ደግሞ ሰዎችን ማነሳሳት (Inspire) ማድረግ ነው ብለህ ነበር፡፡ አንተን በጠዋት አንቅቶ ግጥም እንድትጽፍ የሚያደርግህ ምንድን ነው?
ለምን፡- ሁሌም ከእንቅልፌ ስነቃ ግጥሞችን በማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ እለቃለሁ ይኼን ደግሞ እስክሞት የምቀጥለው ነገር ነው፡፡ ….. ፈጠራ ሙሉ በሙሉ በአርቲስቶች ቁጥጥር የተያዘ አይደለም፡፡ ሁሉም ሰው በራሱ መንገድ ፈጣሪ ነው፡፡ ስለዚህ የእኔ ሥራ መነቃቃትን ወይም ሰዎችን ማንቃት መፈለግ ነው፡፡ መማር እና ማስተማር፡፡
ሪፖርተር፡- መቼ ነው ግጥም መጻፍ እንደምትችል ያወቅከው?
ለምን፡- ለምን የሚለው ስሜ መሆኑን ከማወቄ በፊት መግጠም ጀምሬ ነበር፡፡ ለምን የሚለውን ስም ይዤ እንዴት ገጣሚ መሆን አልችልም፡፡ እንግሊዞቹ የሰጡኝን ስም ይዤ እገጥም ነበር፡፡ ስለዚህ ገጣሚ ሆኜ ነው የተወለድኩት ማለት ይቻላል፡፡
ሪፖርተር፡- እስካሁን ያለህ የቻንስለርነት ቆይታ ምንይመስላል?
ለምን፡- ጥሩ ነው፡፡ ለተማሪዎቼ የተስፋ ምንጭ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ፡፡
ሪፖርተር፡- የራስህ ቤተሰብ የመመሥረት ሐሳብ አለህ?
ለምን፡- ምን አልባት ወደ ፊት፡፡
ሪፖርተር
‹‹ራሴን በእንግሊዝና በኢትዮጵያ መሀል ላይ ያለ ድልድይ አድርጌ ነው የምወስደው››
ገጣሚና ጸሐፊ ለምን ሲሳይ
ትውልደ ኢትዮጵያ ብሪታንያዊው ለምን ሲሳይ ዕውቅ ገጣሚና ጸሐፊ ነው፡፡ በተለያዩ ጥበብ ተኮር ተቋማት እየሠራ ይገኛል፡፡ በሳውዝ ባንክ ማዕከል ተባባሪ አርቲስት፣ በሌተር ቦክስ ክለብ ድጋፍ ሰጪ፣ የቺልድረንስ ሪዲንግ ፈንድ አምባሳደር ሲሆን የክብር ዶክትሬት (ዶክተር ኦፍ ሌተርስ) ተሰጥቶታል፡፡ ለለንደን ኦሊምፒክ ግጥም የደረሰ፣ የበርካታ ተለጣጣቂ መጻሕፍት፣ መጣጥፎች፣ ሪከርዶች ወዘተ ጸሐፊ ነው፡፡ ከሰኔ 2007 ዓ.ም. ጀምሮ የማንችስተር ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆኖ ለሰባት ዓመታት አገልግሎት ተመርጧል፡፡ ኢትዮጵያ ተወልዶ ብሪታኒያ በጉዲፈቻ ያደገው ለምን ሕይወቱን ከአፄ ቴዎድሮስ ልጅ ልዑል ዓለማየሁ ጋር ያገናኘዋል፡፡ የልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ አፅም ወደ አገሩ እንዲመለስ ምኞቱ መሆኑንም ይናገራል፡፡ መሰንበቻውን ወደ ኢትዮጵያ ጎራ ያለውን ለምን ሲሳይን ዳዊት እንደሻው ስለ ዐውደ ሕይወቱ አውግቶታል፡፡
ሪፖርተር፡- በቅድሚያ ስለነበረህ የአንድ ሳምንት ቆይታ እስኪ ግለጽልን፡፡
ለምን፡- እስካሁን የነበረኝ ቆይታ በጣም አዝናኝና ፍሬያማ ነበር፡፡ ከብዙ ሰዎች ጋር የመገናኘቱን ዕድል አግኝቻለሁ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ከሪታ ፓንክረስት ጋር የመገናኘቱን ክብር አግኝቻለሁ፡፡ በተጨማሪም አሉላ ፓንክረስት ጋር ተገናኝቼ ከማንችስተር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት እንዴት የውጭ የትምህርት ዕድል ለኢትዮጵያውያን ማመቻቸት እንደምንችል መክረናል፡፡
እሱ ብቻ አይደለም ከብሪትሽ ካውንስል አዲስ ዳይሬክተር ፒተር ብራውን ጋር ተገናኝተናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከአዲስ አበባና ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ከመጡ ምሁራን ጋርም የመገናኘቱን ዕድልም አግኝቼ ከውጭ የትምህርት ዕድሉ ጋር በተያያዘ እንዴት የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ከማንችስተር ዩኒቨርሲቲ ጋር እንዴት መሥራት እንደሚችሉ ተነጋግረናል፡፡ እንግዲህ እኔ ራሴን በእንግሊዝና በኢትዮጵያ መሀል ላይ ያለ ድልድይ አድርጌ ነው የምወስደው፡፡ አሁን አሁን ጊዜዎች ባለፉ ዕድሜያችንም በገፋ ቁጥር እኔ እዚህ ያለሁት ለምክንያት ነው የሚለው ሐሳብ ሁሌም ይመጣብኛል፡፡ ይኼ ደግሞ ለእኔ መባረክ ነው፡፡ በዚች ታላቅ አገር ውስጥ በሚኖሩ ሰዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ ተቀባይነትን ባገኘሁ ቁጥር በታወኩ ቁጥር ለእኔ ይሄ ትልቅ ነገር ነው፤ ስጦታ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ መሆን ከኢትዮጵያ መፈጠር ትልቅ ስጦታ ነው፡፡
ሪፖርተር፡- እስኪ ደግሞ ወደ ልጅነት ታሪክህ እንመለስ ከኢትዮጵያ ቤተሰቦች ተወለድክ፣ ለእንግሊዛዊ ቤተሰቦች ተሰጠህ እንደገና ደግሞ ተላልፈህ የልጆች ማሳደጊያ ማዕከል ወስጥ አደግክ፡፡ እስኪ ይኼ የልጅነት ጊዜህ የአሁኑን ለምን ሲሳይን በምን መንገድ ቀርጿል?
ለምን፡- ከምንም በላይ ብዙ አሉታዊ ነገሮች ቢያልፉም አሁን ያለሁበት ላይ ደርሻለሁ፡፡ ይህ ማለት ግን ለምን በልጅነቱ በብዙ መጥፎ ነገሮች ስላለፈ በዚህም ምክንያት አሁን ያለበት ጥሩ ደረጃ ላይ ደርሷል ማለት አይደለም፡፡ እርግጥ ነው በብዙ መጥፎ ነገሮች ውስጥ አልፌያለሁ ስለዚህ መጠየቅ ያለብኝ በዚህ ውስጥ እኔ ማን ነኝ? የሚለውን ነው በመጥፎ ነገሮች ውስጥ በማለፌ ንዴት ውስጥ ገባሁ፣ ሌሎችን ጎዳሁ ወይስ ራሴን አደጋ ላይ ጣልኩ? በተቃራኒው የእኔ መገፋት፣ ሕመምና ስቃይ የሌሎችን ሕመም እንድረዳ እንዲሁም የመዳንን ኃይል እንድረዳ አድርጎኛል፡፡ እንደ እኔ የመዳን ኃይል ከመሠረቴ ነው ሥር መሠረቴ ደግሞ ከዚሁ ከኢትዮጵያ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች እንግሊዝ ስላደገ፣ ጥሩ ትምህርት ስለተማረ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሷል ይላሉ ነገር ግን ጥሩ ትምህርት አልነበረኝም ነበር፣ ተጎድቼ ነበር፡፡ እኔ እማውቀው ይኼን ሁሉ አሽንፌ መምጣቴን ነው፡፡ ብዙዎቻችን በቤተሰበ፣ በማኅበረሰብ ውስጥ እንዲሁም በተለያዩ ነገሮች ስናልፍ ብዙ መጥፎ ልምዶች ሊኖሩን ይችላሉ፣ ልንጎዳ እንችላለን፡፡ ነገር ግን ጥያቄው የእኛ መጎዳት ሌሎችን እንድንጎዳ መብት ይሰጠናል ወይ? የእኛ መጎዳት ሌሎችን እንድንጎዳ በፍጹም መብት አይሰጠንም፡፡ በተቃራኒው የእኛ መጎዳት የሌሎችን ሕመም፣ መገፋት እንዲሁም መነጠልን እንድንረዳ ያደርገናል፡፡ ይረዳናል፡፡ ይኼን ያህል ካወቅኩ እኔ ላይ የሆነው ሌሎች ላይ እንዲደገም አልፈልግም፡፡ ማነህ አንተ? እንግሊዛዊ ነህ? አይሪሽ ነህ ወይስ ኤርትራዊ ወይስ ደግሞ ሶማሊያዊ … ለእኔ አንተ ማለት ወንድሜ ነህ እዚህ ላይ በመተማመን አብሮ መሥራት፣ መኖር ይቻላል፡፡
ሪፖርተር፡- እስኪ ከወላጅ እናትህ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ስትግናኙ ስለነበረው ነገር ንገረኝ?
ለምን፡- የሚገርም ስሜት ነበር፡፡ የማርሸት ሲሳይ ወላጅ እናቴ በጣም የምትገርምና ጠንካራ ሴት ነች፡፡ እንደ አብዛኛው 1950ዎቹ 60ዎች ትውልድ ለትምህርት ወደ ውጭ የመሄድ ዕድል አግኝታ ነበር፡፡ በዚያ ጊዜ ለትምህርት ወደ ውጭ የሄዱት የእናቴ ዓይነት ወጣቶች በዚያን ጊዜ የነበረውን የኢትዮጵያ መንፈስ ይዘው ዓለምን ዞረዋል፡፡ በጊዜው እናቴ እኔን አረገዘች ከዚያ ለጉዲፈቻ ሰጠችኝ፡፡ ብዙ ሰው የማያውቀው እናቴ ተመልሳ እኔን ለማግኘት ሞክራ እንደነበር ነው፡፡ እኔ ለሕፃናት ማዕከሉ በጻፈችው ደብዳቤ ልጇን እንደምትፈልግ፣ ልጇ በአገሩ እንዲያድግ እንደምትፈልግና በሰው አገር መገለል እንዳይደርስበት ገልጻ ነበር፡፡ በጊዜው እናቴ 21 ዓመቷ ነበር፡፡ እናቴ የሚቻላትን አድርጋ ነበር ግን እንግሊዞቹ መልሰው እኔን ሊሰጧት አልፈለጉም፡፡
ሪፖርተር፡- ለእናትህ አስቸጋሪ ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል?
ለምን፡- በጣም እንጂ ማሰቡ ራሱ ይከብዳል፡፡ ከዚያ እናቴ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰች፣ መመለስም ነበረባት ምክንያቱም በጊዜው አባቷ ታመው ነበር ከዚያም አቶ አሸናፊ ሽፈራውን አገባች፡፡ ከዚያም ከአምስት ዓመት በኋላ ደርግ ሥልጣን ያዘ፣ ባሏ ታሰረ፡፡ ስለዚህ ለሕይወቷ ስትል አገሩን ለቃ መሄድ ነበረባት፡፡ ጠንካራ ሴት ነበረች፡፡ ከብዙ ዓመት በኋላ 21 ዓመት ሲሆነኝ እናቴን አገኘሁ፡፡ ቀላል አልነበረም በእውነቱ፣ በጊዜው እሷን ማግኘት ውብ ነበር፡፡ እሷን ማግኘት ወደ ቤት እንደመመለስ ነበር ወደ ኢትዮጵያ፡፡
ሪፖርተር፡- ኢትዮጵያ ውስጥ ተወልጄ፣ አድጌ ቢሆን ብለህ ታውቃለህ?
ለምን፡- እሱንማ በምን ዕድሌ፡፡ ሁሌም የምፈልገው ነው ግን ደግሞ ማግኘት ያልቻልኩት ነው፡፡ ስለዚህ ያለኝን መቀበልና ባለኝ ነገር መኖር ነው፡፡ እውነቱን ለመቀበል በልጅነቴ የሚያውቁኝ እናት፣ አባት እንዲሁም እህትና ወንድም የለኝመ፡፡ ትልቁን የሕይወት ዘመኔን ሕልምና ምኞት ልንገርህ? የልዑል ዓለማየሁ አፅም ወደ አገሩ ሲመለስ ማየት ለእኔ ትልቅ ነገር ነው፡፡ ሕይወቱ ከእኔ ጋር ይገናኛል ብዬ አስባለሁ፡፡
ሪፖርተር፡- ስለዚህ የእሱ ሕይወት ከአንተ ጋር ይገናኛል ብለህ ታስባለህ ማለት ነው?
ለምን፡- በእንግሊዞች ከአገሩ ተወስዷል፡፡ አሥራ ስምንት ዓመት እስኪሞላው በካፒቴን ስፒዲ ሥር ሆኖ አድጓል፣ ከዚያም ሊድስ ወደ ተባለ ሰሜን ኢንግላንድ ወሰዱት፡፡ ከዚያም በዓመት ውስጥ ሞተ፡፡ እንደሚሉት ሞቱ የተፈጥሮ ሞት ነው ይላሉ፡፡ ለእኔ ይኼ አይዋጥልኝም፡፡ የሆነ ነገር ነበር የሆነ! ብዙ መጠናት ያለባቸው ብዙ የማናውቃቸው ነገሮች አሉ፡፡ እኔ ወደ አገሬ እንደተመለስኩ እሱም እንዲመለስ እፈልጋለሁ፡፡
ሪፖርተር፡- ራስህን ማን ነኝ የምትለው?
ለምን፡- ኢትዮጵያዊ፣ እንግሊዛዊ፣ የዓለም ዜጋ፣ የሞሎኪሎች የመንፈሶች ስብስብ፡፡
ሪፖርተር፡- ስለራስህ ስናነሳ ብዙ ሰዎች በኢትዮጵያ እንግሊዝኛ ማንበብም ሆነ መረዳት አይችሉም ሥራህን ለመተርጎም ያሰብከው ነገር አለ?
ለምን፡- የተወጠኑ ነገሮች አሉ እስካሁን ባይሳኩም፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት ከኤፍሬም ሥዩም ጋር አብረን እየሠራን ነው፡፡ ጥሩ የቋንቋ ችሎታ ያለው የጥበብ ሰው ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ገጣሚዎች ኤፍሬምን እንዲሁም የበውቀቱ ስዩምን ሥራዎች አደንቃለሁ፡፡ ትልቅ የሥነ ግጥም ሀብት ያለበት አገር ነው፡፡
ሪፖርተር፡- ብዙ ጊዜ ስለ መነሳሳት ወይም መነቃቃት ትናገራለህ፡፡ በአንዱም ንግግር የአንተ ዓላማ በሰዎች መነሳት ወይም ደግሞ ሰዎችን ማነሳሳት (Inspire) ማድረግ ነው ብለህ ነበር፡፡ አንተን በጠዋት አንቅቶ ግጥም እንድትጽፍ የሚያደርግህ ምንድን ነው?
ለምን፡- ሁሌም ከእንቅልፌ ስነቃ ግጥሞችን በማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ እለቃለሁ ይኼን ደግሞ እስክሞት የምቀጥለው ነገር ነው፡፡ ….. ፈጠራ ሙሉ በሙሉ በአርቲስቶች ቁጥጥር የተያዘ አይደለም፡፡ ሁሉም ሰው በራሱ መንገድ ፈጣሪ ነው፡፡ ስለዚህ የእኔ ሥራ መነቃቃትን ወይም ሰዎችን ማንቃት መፈለግ ነው፡፡ መማር እና ማስተማር፡፡
ሪፖርተር፡- መቼ ነው ግጥም መጻፍ እንደምትችል ያወቅከው?
ለምን፡- ለምን የሚለው ስሜ መሆኑን ከማወቄ በፊት መግጠም ጀምሬ ነበር፡፡ ለምን የሚለውን ስም ይዤ እንዴት ገጣሚ መሆን አልችልም፡፡ እንግሊዞቹ የሰጡኝን ስም ይዤ እገጥም ነበር፡፡ ስለዚህ ገጣሚ ሆኜ ነው የተወለድኩት ማለት ይቻላል፡፡
ሪፖርተር፡- እስካሁን ያለህ የቻንስለርነት ቆይታ ምንይመስላል?
ለምን፡- ጥሩ ነው፡፡ ለተማሪዎቼ የተስፋ ምንጭ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ፡፡
ሪፖርተር፡- የራስህ ቤተሰብ የመመሥረት ሐሳብ አለህ?
ለምን፡- ምን አልባት ወደ ፊት፡፡
ሪፖርተር
0 Comments
0 Shares