የባንክና የኢንሹራንስ ኩባንያ ኃላፊዎች የሚሾሙበት መሥፈርት ሊሻሻል ነው
በዳዊት እንደሻውየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ላለፉት አምስት ዓመታት ያህል የባንክና የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ዋናና ምክትል ሥራ አስፈጻሚዎችን ሹመት ሲመዝንና ሲያፀድቅበት የነበረውን መሥፈርት ሊያሻሽል ነው፡፡ ከሳምንት በፊት ረቂቅ ማሻሻያ መመርያ ለባንክና ለኢንሹራንስ ኩባንያዎች ለአስተያየት ቀርቦ ለብሔራዊ ባንክ ተመልሷል፡፡የተሻሻለው ረቂቅ መመርያ ቀድሞ ከነበረው መመርያ የተለያዩ ለውጦችን ይዞ ብቅ ያለ ሲሆን፣ በአንዳንዶቹ ላይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የባንክ ኃላፊዎች ቅሬታቸውን አቅርበዋል፡፡በረቂቅ መመርያው መሠረት አንድ ተሿሚ የባንክ ወይም የኢንሹራንስ ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለመሆን በምክትልነት ለአምስት ዓመታት ያገለገለ የሚል ሲሆን፣ ቀድሞ በነበረው መመርያ ግን ለአምስት ዓመታት በባንክ