የቆሼ ተጎጂዎች ማቋቋሚያ ፓኬጅ በተለያዩ ምክንያቶች መጓተቱ ተገለጸ
ከ94.8 ሚሊዮን ብር በላይ ዕርዳታ መሰብሰቡ ተጠቁሟልለቆሼ ተጎጂዎች እንዲውል በተዘጋጀው የማቋቋሚያ ፓኬጅ ያላግባብ ለመጠቀም በገቡ ሰዎች፣ በቤተሰብ መካከል በተነሱ የይገባኛል ጥያቄዎችና ተጎጂዎች መረጃዎቻቸውን በአግባቡ አሟልተው ባለማቅረባቸው በሥራው ላይ መንጓተት እንዲፈጠር ምክንያት መሆናቸው ተገለጸ፡፡ ያላግባብ ለመጠቀም በገቡ 166 ሰዎች ላይም አስተዳደራዊ ውሳኔ መሰጠቱና በሕግ እንዲጠየቁ ለማድረግም ምርመራ እየተካሄደባቸው የሚገኙ እንዳሉ ታውቋል፡፡ ፍርድ ቤት ለተለያዩ ሁለት ሰዎች የወራሽነት መብት በመስጠቱ ጭቅጭቅ ያስነሳ ጉዳይም መኖሩ ተጠቁሟል፡፡ ‹‹በደንብ መታየት ያለባቸው የይገባኛል ጥያቄዎች ያላቸው ጉዳዮች አሉ፤›› የሚሉት የአዲስ አበባ ከተማ ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ