አርሰናሎች ጋቦናዊውን የዶርትሞንድ ተጫዋች ኤምሬክ ኦቦሚያንግን ከፈለጉ የግድ ከሀምሳ ሚሊየን ፓውንድ በላይ ማውጣት አለባቸው የሚሉ ዘገባዎች ቢወጡም መድፈኞቹ ግን አጥቂውን እንደሚያስፈርሙት እርግጠኞች ሆነዋል ሲሉ የተለያዩ ዘገባዎች እያመላከቱ ይገኛሉ።ባለፈው አርብ የዶርትሞንዱ የስፖርት ዳይሬክተር ሚካኤል ዞርክ አርሰን ቬንገር ለኦቦሚያንግ ያላቸው ግምት ዝቅተኛ ነው ብለው የሰጡትን አስተያየት ተከትሎ ሁኔታዎች የተወሳሰቡ ቢመስሉም አሁነም  በጋቦኒያዊው ተጫዋች ዙሪያ ሁለቱ ከክለቦች ድርድር […]
The post ከስፖርት ማዕድ_አጫጭር የውጪ ስፖርታዊ መረጃዎች appeared first on Ethiopian News Portal! News.et.
አርሰናሎች ጋቦናዊውን የዶርትሞንድ ተጫዋች ኤምሬክ ኦቦሚያንግን ከፈለጉ የግድ ከሀምሳ ሚሊየን ፓውንድ በላይ ማውጣት አለባቸው የሚሉ ዘገባዎች ቢወጡም መድፈኞቹ ግን አጥቂውን እንደሚያስፈርሙት እርግጠኞች ሆነዋል ሲሉ የተለያዩ ዘገባዎች እያመላከቱ ይገኛሉ።ባለፈው አርብ የዶርትሞንዱ የስፖርት ዳይሬክተር ሚካኤል ዞርክ አርሰን ቬንገር ለኦቦሚያንግ ያላቸው ግምት ዝቅተኛ ነው ብለው የሰጡትን አስተያየት ተከትሎ ሁኔታዎች የተወሳሰቡ ቢመስሉም አሁነም  በጋቦኒያዊው ተጫዋች ዙሪያ ሁለቱ ከክለቦች ድርድር […] The post ከስፖርት ማዕድ_አጫጭር የውጪ ስፖርታዊ መረጃዎች appeared first on Ethiopian News Portal! News.et.
NEWS.ET
ከስፖርት ማዕድ_አጫጭር የውጪ ስፖርታዊ መረጃዎች
1-አርሰናሎች ጋቦናዊውን የዶርትሞንድ ተጫዋች ኤምሬክ ኦቦሚያንግን ከፈለጉ የግድ ከሀምሳ ሚሊየን ፓውንድ በላይ ማውጣት አለባቸው የሚሉ ዘገባዎች ቢወጡም መድፈኞቹ ግን አጥቂውን እንደሚያስፈርሙት እርግጠኞች ሆነዋል ሲሉ የተለያዩ ዘገባዎች እያመላከቱ ይገኛሉ።ባለፈው አርብ የዶርትሞንዱ የስፖርት ዳይሬክተር ሚካኤል ዞርክ አርሰን ቬንገር ለኦቦሚያንግ ያላቸው ግምት ዝቅተኛ ነው ብለው የሰጡትን አስተያየት ተከትሎ ሁኔታዎች የተወሳሰቡ ቢመስሉም አሁነም  በጋቦኒያዊው ተጫዋች ዙሪያ ሁለቱ ከክለቦች ድርድር ላይ መሆናቸው ታውቋል።ዶርትሞንዶች ደምበሌን ለባርሴሎና ከመሸጣቸው በፊተ የተከተሉትን መንገድ በኦቦሚያንግ ላይም የሚተገብሩ ከሆነ አርሰናሎች ሊቸገሩ እንደሚችሉ ተገመቷል። ሆኖም ግን እንደተባለው መድፈኞቹ ለጋቦናዊው ዝውውር ከሀምሳ ሚሊየን ፓውንድ በላይ ለማውጣት ከወሰኑ በላካዜት የተያዘው ሪከርድ የዝውውር ሂሳብ በስሙ የሚረከብ ነው የሚሆነው። 2-የቼልሲው ድንቅ ቤልጄማዊ ተጫዋች ኤዲን ሃዛርድ ቼልሲ በጥር የዝውውር መስኮት ወደ ክለቡ ለመቀላቀለ ባሰባቸው አዳዲስ ፈራሚዎች ደስተኛ አለመሆኑን ተናግሯል። ሃዛርድ በክለቡ ውስጥ በቂ የሚባሉ የአጥቂ መስመር ተጫዋቾች እንዳሉ ገልፆ በነሱ በሚገባ መጠቀም እየተቻለ አላግባብ የሆነ ዝውውር ማከናወን አስፈላጊ አለመሆኑን አመልክቷል።በአንፃሩ ጣሊያናዊው አሰልጣኘ አንቶኒዮ ኮንቴ ቼልሲ አመራሮች ላይ በሚከተሉት የዝውውር መንገድ ድስተኛ ባለመሆናቸው በክረምቱ የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ሊሰናበቱ እንደሚችሉ በሰፊው እየተነገረ ይገኛል። 3- የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በሳንቼዝ ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።ሳንቼዝ በዩድንሴ እያለ ቺሊያዊን ለማስፈረም ፈላጎት አሳይተው የነበሩት ፈርጌ ሳንቼዝን ለረጅም ጊዜ እንከታተለው ነበር።ወደሗላ መለስ ብለንም ታሪኩን ለማጥናት ሞክረናል። ነገር አርብ በውቅቱ ሊሳካልን አልቻለም።ላለፉት አመታት ምርጥ ምርጥ ቺሊያዊ ተጫዋቾችን ተመልከተናል። ሳንቼዝም ከነሱ አንደኛው ነው።_ ሲሉ ቆፈጣናው የቀድሞ የዩናይትድ አሰልጣኝ አሌክስ ፈርጉሰን ተናግረዋል። 4- ሮቢን ቫንፐርሲ ውድ ቀድሞ ክለቡ ፌይኖርድ በአስራ ስምንት ወራት ኮንትራት ተመልሷል። የቀድሞ የአርሰናልና የማንቸስተር ዩናይትድ አጥቂ የቀድሞው የቡድን አጋሩን ቫምፐሮኮስትን በፌይኖርድ በአሰልጣኝነት ዳግመኛ የሚያገኘው ነው የሚሆነው። ሆላንዳዊው የሰላሳ አመት ተጫዋች ከመድፈኞቹ ቀያይ ሰይጣኖቹን በፈርጉሰን አሰልጣኝነት ዘመን በመቀላቀል ዩናይትድ ከሲቲ የቻምፒዮንነቱን ክብር እንዲያስመልስ ትልቅ አስተዋፅኦ ማበርከቱ ይታወሳል። የሮተርዳሙ ክለብ ፌይኖርድም በዌብሳይቱ የቫንፕርሲን ዝውውር ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል።ቫንፐርሲ ማንቸስተር ዩናይትድን ከለቀቀ በኃላ ወደ ቱርኩ ፌነርባቼ ማምራቱ ይታወሳል። 5- የሊቨርፑሉ የፊት መስመር ተጫዋች ዳንኤል ስቶሬጅ በውሰት ውል ቀዮቹን ሊለቅ እንደሚችል ዴይሊ ሜይል አስነብቧል። ስቶሬጅ ከዲሴምበር በኃላ በሜዳ ላይ ያልታየ ሲሆን በአንፊልድም ደስተኛ አለመሆኑ በተደጋጋሚ ሲነገር ቆይቷል። የስፔኑ ክለብ ሲቪላም ተጫዋቹን በውሰት ውል ለማዘዋውር ፍቃደኛነቱን ያሳየ ሲሆን ሳምነታዊ ደሞዙነም ለመክፈል ተስማምቷል ነው የተባለው።
0 Comments 0 Shares