ቢጂአይ ኢትዮጵያ ዘቢዳር ቢራን ሊገዛ ነው
በቅርቡ የራያ ቢራን አክሲዮኖች ለመጠቅለል ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበው ቢጂአይ ኢትዮጵያ፣ በተመሳሳይ መንገድ የዘቢዳር ቢራን አክሲዮኖች ለመግዛት ጫፍ መድረሱ ታወቀ፡፡
የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት፣ ቢጂአይ ኢትዮጵያ የዘቢዳር ቢራን አክሲዮኖች ለመግዛት ባቀረበው ሐሳብ በመሠረት ከዘቢዳር ቢራ ዋነኛ ባለአክሲዮን ከሆነው የቤልጂሙ ዩኒቢራ ጋር በአክሲዮኖች ሽያጭ ላይ ሲደራደር ቆይቷል፡፡
ቢጂአይ የዘቢዳር ቢራ አክሲዮኖችን ለመግዛት ያቀረበው ዋጋ ለጊዜው ባይገለጽም፣ የራያ ቢራን አክሲዮኖች ለመግዛት ካቀረበው ዋጋ ጋር ተቀራራቢ እንደሚሆን ተሰምቷል፡፡ በሌላ በኩል ዘቢዳር ማምረት ከጀመረ በቅርቡ በመሆኑና የኢንቨስትመንት ወጪው ያነሰ ስለሆነ፣ ለአክሲዮኖች ግዥ የሚሰጠው ዋጋ ከራያ ቢራ ያነሰ እንደሚሆን እየተገለጸ ነው፡፡
ከሁለቱም ወገኖች የአክሲዮኖችን ሽያጭ በተመለከተ ለጊዜው መረጃ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ ባይሳካም፣ በሽያጩ ላይ ግን ድርድር እየተደረገ መሆኑንና በሒደትም ስምምነት ላይ እየተደረሰ እንደሆነ ከውስጥ አዋቂ ምንጮች ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
የዘቢዳር ቢራ አክሲዮን ማኅበር 60 በመቶ የተያዘው በቤልጂየሙ ዩኒቢራ ሲሆን፣ 40 በመቶው ደግሞ የዥማር ሁለገብ ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማኅበር ነው፡፡ አክሲዮን ማኅበሩ ከ2,000 በላይ ባለአክሲዮኖች ሲኖሩት፣ በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ የተሰማራ ነው፡፡ በኮንስትራክሽን፣ በሪል ስቴትና በመሳሰሉት መስኮ ይሳተፋል፡፡
ዘቢዳር ቢራ ከአዲስ አበባ 167 ኪሎ ሜትር ርቀት ወልቂጤ ከተማ ገባ ብላ በምትገኘው ጉብሬ ውስጥ የተገነባ ፋብሪካ ነው፡፡
በዓመት 350 ሺሕ ሔክቶ ሊትር የማምረት አቅም ያለው ይህ ፋብሪካ ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት ሲሆን፣ ወደ ገበያ የገባው በታኅሳስ 2009 ዓ.ም. እንደነበር ይታወሳል፡፡
ቢጂአይ ኢትዮጵያ የራያ ቢራ አክሲዮኖችን ሙሉ በሙሉ ለመግዛት ያቀረበው ጠቅላላ ዋጋ 2.5 ቢሊዮን ብር እንደነበር መዘገባችን አይዘነጋም፡፡ ይህ ዋጋ ለአንድ አክሲዮን ሰባት እጥፍ ዋጋ የሰጠ ነው፡፡
በቅርቡ የራያ ቢራን አክሲዮኖች ለመጠቅለል ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበው ቢጂአይ ኢትዮጵያ፣ በተመሳሳይ መንገድ የዘቢዳር ቢራን አክሲዮኖች ለመግዛት ጫፍ መድረሱ ታወቀ፡፡
የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት፣ ቢጂአይ ኢትዮጵያ የዘቢዳር ቢራን አክሲዮኖች ለመግዛት ባቀረበው ሐሳብ በመሠረት ከዘቢዳር ቢራ ዋነኛ ባለአክሲዮን ከሆነው የቤልጂሙ ዩኒቢራ ጋር በአክሲዮኖች ሽያጭ ላይ ሲደራደር ቆይቷል፡፡
ቢጂአይ የዘቢዳር ቢራ አክሲዮኖችን ለመግዛት ያቀረበው ዋጋ ለጊዜው ባይገለጽም፣ የራያ ቢራን አክሲዮኖች ለመግዛት ካቀረበው ዋጋ ጋር ተቀራራቢ እንደሚሆን ተሰምቷል፡፡ በሌላ በኩል ዘቢዳር ማምረት ከጀመረ በቅርቡ በመሆኑና የኢንቨስትመንት ወጪው ያነሰ ስለሆነ፣ ለአክሲዮኖች ግዥ የሚሰጠው ዋጋ ከራያ ቢራ ያነሰ እንደሚሆን እየተገለጸ ነው፡፡
ከሁለቱም ወገኖች የአክሲዮኖችን ሽያጭ በተመለከተ ለጊዜው መረጃ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ ባይሳካም፣ በሽያጩ ላይ ግን ድርድር እየተደረገ መሆኑንና በሒደትም ስምምነት ላይ እየተደረሰ እንደሆነ ከውስጥ አዋቂ ምንጮች ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
የዘቢዳር ቢራ አክሲዮን ማኅበር 60 በመቶ የተያዘው በቤልጂየሙ ዩኒቢራ ሲሆን፣ 40 በመቶው ደግሞ የዥማር ሁለገብ ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማኅበር ነው፡፡ አክሲዮን ማኅበሩ ከ2,000 በላይ ባለአክሲዮኖች ሲኖሩት፣ በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ የተሰማራ ነው፡፡ በኮንስትራክሽን፣ በሪል ስቴትና በመሳሰሉት መስኮ ይሳተፋል፡፡
ዘቢዳር ቢራ ከአዲስ አበባ 167 ኪሎ ሜትር ርቀት ወልቂጤ ከተማ ገባ ብላ በምትገኘው ጉብሬ ውስጥ የተገነባ ፋብሪካ ነው፡፡
በዓመት 350 ሺሕ ሔክቶ ሊትር የማምረት አቅም ያለው ይህ ፋብሪካ ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት ሲሆን፣ ወደ ገበያ የገባው በታኅሳስ 2009 ዓ.ም. እንደነበር ይታወሳል፡፡
ቢጂአይ ኢትዮጵያ የራያ ቢራ አክሲዮኖችን ሙሉ በሙሉ ለመግዛት ያቀረበው ጠቅላላ ዋጋ 2.5 ቢሊዮን ብር እንደነበር መዘገባችን አይዘነጋም፡፡ ይህ ዋጋ ለአንድ አክሲዮን ሰባት እጥፍ ዋጋ የሰጠ ነው፡፡
