የፓርላማ አባላትን በቁጭት ያንገበገበው የኦሮሚያና የሶማሌ ግጭት ሪፖርት
ዮሐንስ አንበርብር
Sun, 01/07/2018 - 11:49
የፓርላማ አባላትን በቁጭት ያንገበገበው የኦሮሚያና የሶማሌ ግጭት ሪፖርት ዮሐንስ አንበርብር Sun, 01/07/2018 - 11:49
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COM
የፓርላማ አባላትን በቁጭት ያንገበገበው የኦሮሚያና የሶማሌ ግጭት ሪፖርት | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኦሮሚያና የሶማሌ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎችን ግጭት እንዲያጣራ የተዋቀረው የሱፐርቪዥን ቡድን ሪፖርቱን ያቀረበው ሐሙስ ታኅሳስ 26 ቀን 2010 ዓ.ም. ነበር፡፡ በሁለቱ ክልሎች የተሰማራው የሱፐርቪዥን ቡድን በአካል ተገኝቶ እስከ ኅዳር 2010 ዓ.ም. ድረስ ከተፈናቃዮችና ከአካባቢ አመራሮች የሰበሰበውን መረጃ በዝርዝር አቅርቧል፡፡ ተፈናቃዮች በግጭቱ ወቅት በደረሱባቸው ጉዳትና እንግልት፣ የንብረት ዘረፋና የተለያዩ ጥቃቶች ለጤናና ለሥነ አዕምሮ ቀውስ መዳረጋቸው ተገልጿል፡፡ መንግሥት ግጭቱን ለማስቆም ካለመቻሉም በላይ ችግሩ ከተፈጠረ በኋላ ፈጥኖ ዕርምጃ ባለመወስዱ፣ እንዲሁም የመንግሥት አመራሮች ለግጭቱ መፍትሔ ባለመስጠታቸው ተስፋ መቁረጣቸው ተመልክቷል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም ከሕገ መንግሥቱ በተፃራሪ ግፍና በደል ሲደርስ ድምፃቸውን ባለማሰማታቸው ተወቅሰዋል፡፡ ዝርዝር ሪፖርቱ ከቀረበ በኋላ የፓርላማ አባላት በቁጭት በመንገብገብ ጥያቄዎች አቅርበዋል፡፡
Like
2
0 Comments 0 Shares