በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ አንዳንድ የሂሳብ ባለሙያዎች የሙያ ፍቃድ ማግኘት አልቻልንም አሉ።

ቅሬታቸውን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያቀረቡት ባለሞያዎች፥ ላለፉት 2 ዓመታት ፍቃድ ለማግኝት ቢጠይቁም እንዳላገኙ ነው የተናገሩት።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ የፍቃድ አሰጣጥ ሂደቱ ወጥነት ያለው እና የተደራጀ ባለመሆኑም በተለይ ከግብር ጋር ተያይዞ የሚሰሩ ህገ ወጥ የሂሳብ አሰራር ሀገሪቱን በእጅጉ እየጎዳ ነው ይላሉ።

ይህን ቅሬታ ይዞ ወደ አዲስ አበባ ኦዲት ቢሮ ያቀናው ፋና ብሮድ ካስቲንግ ኮርፖሬት፥ ተቋሙ በመቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 29/2004 የኦዲትና ሂሳብ ሙያ ፍቀደ ለመስጠት የውክልና ስልጣን የተሰጠው ቢሆንም፤ ለተቋሙ ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ በአዋጅ ሳይሻር የሙያ ፍቃድ እንዳይሰጥ መታገዱን ነው ከቢሮው ማረጋገጥ የቻለው።

የተቋሙ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ተረፈ፥ ቢሮው የሙያ ፍቃድ ለመስጠት ዝግጅት አጠናቆ ምዝገባ በጀመረበት ሁኔታ ላይ እያለ ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት የእገዳ ደብዳቤ እንደደረሰው ያስረዳሉ።

አሁንም ድረስ ኦዲት ቢሮው በአዋጅ የተፈቀደለትን ሀላፊነት ለመወጣት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በተለይ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ጋር ቢነጋገርም የተሰጠው ቀጥተኛ ምላሽ እንደሌለ ነው የገለጸው።

ጉዳዩ ይምለከተዋል የተባለውና የሙያ አገልግሎት ለሚሰጡ ድርጅቶች ፍቃድ የመስጠት፣ የመመዝገብ፣ አፈጻጸማቸውን መከታተልና መቆጣጠር ስልጣን የተሰጠው የኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝ እና ኦዲት ቦርድም ፍቃድ መስጠት አልችልም ብሏል።

የቦርዱ የትምህርት ስልጠናና የሙያ ማጎልበቻ ዳይሬክተር ዶክተር ናቃቸው ባሾ፥ ቦርዱ የሂሳብ ሙያ ማረረጋገጫ ሰርተፍኬት እንጂ ፍቃድ መስጠት ስልጣኑ አይደለም ብለዋል።

የኦዲትና ሂሳብ ሙያ ፍቀድ የሚሰጠውን ተቋም አስቆመ የተባለው የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት፣ በግልባጭ ደብዳቤ የደረሳቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አፈጉባኤ ጽህፈት ቤትና የፋይናንስ ቢሮ በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆኑም።
በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ አንዳንድ የሂሳብ ባለሙያዎች የሙያ ፍቃድ ማግኘት አልቻልንም አሉ። ቅሬታቸውን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያቀረቡት ባለሞያዎች፥ ላለፉት 2 ዓመታት ፍቃድ ለማግኝት ቢጠይቁም እንዳላገኙ ነው የተናገሩት። ቅሬታ አቅራቢዎቹ የፍቃድ አሰጣጥ ሂደቱ ወጥነት ያለው እና የተደራጀ ባለመሆኑም በተለይ ከግብር ጋር ተያይዞ የሚሰሩ ህገ ወጥ የሂሳብ አሰራር ሀገሪቱን በእጅጉ እየጎዳ ነው ይላሉ። ይህን ቅሬታ ይዞ ወደ አዲስ አበባ ኦዲት ቢሮ ያቀናው ፋና ብሮድ ካስቲንግ ኮርፖሬት፥ ተቋሙ በመቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 29/2004 የኦዲትና ሂሳብ ሙያ ፍቀደ ለመስጠት የውክልና ስልጣን የተሰጠው ቢሆንም፤ ለተቋሙ ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ በአዋጅ ሳይሻር የሙያ ፍቃድ እንዳይሰጥ መታገዱን ነው ከቢሮው ማረጋገጥ የቻለው። የተቋሙ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ተረፈ፥ ቢሮው የሙያ ፍቃድ ለመስጠት ዝግጅት አጠናቆ ምዝገባ በጀመረበት ሁኔታ ላይ እያለ ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት የእገዳ ደብዳቤ እንደደረሰው ያስረዳሉ። አሁንም ድረስ ኦዲት ቢሮው በአዋጅ የተፈቀደለትን ሀላፊነት ለመወጣት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በተለይ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ጋር ቢነጋገርም የተሰጠው ቀጥተኛ ምላሽ እንደሌለ ነው የገለጸው። ጉዳዩ ይምለከተዋል የተባለውና የሙያ አገልግሎት ለሚሰጡ ድርጅቶች ፍቃድ የመስጠት፣ የመመዝገብ፣ አፈጻጸማቸውን መከታተልና መቆጣጠር ስልጣን የተሰጠው የኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝ እና ኦዲት ቦርድም ፍቃድ መስጠት አልችልም ብሏል። የቦርዱ የትምህርት ስልጠናና የሙያ ማጎልበቻ ዳይሬክተር ዶክተር ናቃቸው ባሾ፥ ቦርዱ የሂሳብ ሙያ ማረረጋገጫ ሰርተፍኬት እንጂ ፍቃድ መስጠት ስልጣኑ አይደለም ብለዋል። የኦዲትና ሂሳብ ሙያ ፍቀድ የሚሰጠውን ተቋም አስቆመ የተባለው የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት፣ በግልባጭ ደብዳቤ የደረሳቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አፈጉባኤ ጽህፈት ቤትና የፋይናንስ ቢሮ በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆኑም።
0 Comments 0 Shares