• ከጣና ሃይቅ እስከ ጭስ አባይ ፏፏቴ ባለው የአባይ ወንዝ ዳርቻ ላይ ዓለም አቀፍ የማራቶን መሮጫ ሊሰራ ነው፡፡ ናይል ማራቶን የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ የመሮጫ ስፍራ በሀገር አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ ለሚደረግ የማራቶን ሩጫ ውድድር እንዲያገለግል ታስቦ የሚሰራ ሲሆን የዲዛይን ጥናቱን ከባህርዳር ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን አባ የአርክቴክት ስራዎች ድርጅት ማጠናቀቁን የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ አዲስ አዱኛ ተናግረዋል፡፡
    ናይል ማራቶን ከሚሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ ወደ ባህርዳር ከተማ የሚመጡ ቱሪስቶችን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ይጨምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ማራቶንን ጨምሮ በረጅም ርቀት የሩጫ ውድድር የሚታወቁ አትሌቶች ባለቤት ብትሆንም ለማራቶን የመሮጫ ስፍራ ባለመኖሩ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እያገኘች እንዳልሆነ የሚያብራሩት ስራ አስኪያጁ አቶ አዲስ ስራው በሚከናወንበት የወንዙ ዳርቻ እና በአጠቃላይ በፓርኩ ውስጥ የሚገኙ ብርቅዬ እንስሳትን ለመጎብኘት እድል የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
    ሩጫው የሚጀመርበት የጣና ሃይቅ ዳርቻና የሚጠናቀቅበት የጭስ አባይ ፏፏቴ ልዩ መስህብ ያላቸው ስፍራዎች በመሆናቸው ተሳታፊዎች ውድድሩን የበለጠ እንዲወዱት የሚያደርግ ቦታ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ የባህርዳር ከተማ ከንቲባም በበኩላቸው ይህ ፕሮጀክት ለከተማዋ የበለጠ ድምቀት የሚሰጥ እና በቱሪዝም ዘርፍ ገቢ ለማግኘት የሚረዳ በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ለማከናወን በዝግጅት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም ልዩ ልዩ ዘመናዊ ድልድዮችም የግንባታው አካል እንደሚሆኑ ተጠቁሟል፡፡
    ምንጭ፡ዛሚ ኤፍኤም
    ከጣና ሃይቅ እስከ ጭስ አባይ ፏፏቴ ባለው የአባይ ወንዝ ዳርቻ ላይ ዓለም አቀፍ የማራቶን መሮጫ ሊሰራ ነው፡፡ ናይል ማራቶን የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ የመሮጫ ስፍራ በሀገር አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ ለሚደረግ የማራቶን ሩጫ ውድድር እንዲያገለግል ታስቦ የሚሰራ ሲሆን የዲዛይን ጥናቱን ከባህርዳር ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን አባ የአርክቴክት ስራዎች ድርጅት ማጠናቀቁን የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ አዲስ አዱኛ ተናግረዋል፡፡ ናይል ማራቶን ከሚሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ ወደ ባህርዳር ከተማ የሚመጡ ቱሪስቶችን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ይጨምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ማራቶንን ጨምሮ በረጅም ርቀት የሩጫ ውድድር የሚታወቁ አትሌቶች ባለቤት ብትሆንም ለማራቶን የመሮጫ ስፍራ ባለመኖሩ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እያገኘች እንዳልሆነ የሚያብራሩት ስራ አስኪያጁ አቶ አዲስ ስራው በሚከናወንበት የወንዙ ዳርቻ እና በአጠቃላይ በፓርኩ ውስጥ የሚገኙ ብርቅዬ እንስሳትን ለመጎብኘት እድል የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሩጫው የሚጀመርበት የጣና ሃይቅ ዳርቻና የሚጠናቀቅበት የጭስ አባይ ፏፏቴ ልዩ መስህብ ያላቸው ስፍራዎች በመሆናቸው ተሳታፊዎች ውድድሩን የበለጠ እንዲወዱት የሚያደርግ ቦታ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ የባህርዳር ከተማ ከንቲባም በበኩላቸው ይህ ፕሮጀክት ለከተማዋ የበለጠ ድምቀት የሚሰጥ እና በቱሪዝም ዘርፍ ገቢ ለማግኘት የሚረዳ በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ለማከናወን በዝግጅት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም ልዩ ልዩ ዘመናዊ ድልድዮችም የግንባታው አካል እንደሚሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ምንጭ፡ዛሚ ኤፍኤም
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • ካናዳው ኢሲሲ ኩባንያ በኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ የሚሰራ ተሽከርካሪ ለማምረት ጥናት መጀመሩን ገለጸ።
    የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አክሊሉ ኃይለሚካኤል የኩባንያውን ተወካይ ሚስተር ጆርዳን ኦክስሌይን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
    ከውይይቱ በኃላ ሚስተር ጆርዳን እንደገለፁት ኩባንያቸው በኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን የማምረት ፍላጎት አለው።
    ኩባንያቸው ይህንን ማምረት የሚያስችለውን ጥናት መጀመሩንና በተለይም ኢትዮጵያ እየገነባችው ካለው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ጋር የሚጣጣምና የሚሄድ መሆኑን ተናግረዋል።
    ኢትዮጵያ ትልቅ አገር መሆኗ፣ የተማረ ወጣት የሰው ኃይል በብዛት የሚገኝባትና የአየር ንብረትን ለማይበክል የኃይል ምንጭ የሚደረጉ ማበረታቻዎችና ርካሽ የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንደሚያደርጋትም ነው የተናገሩት።
    በእንፋሎት ኤሌክትሪክ ኃይል ኢንቨስትመንት ከመሳተፍ በሻገር ወደ ፊት በሶላር ቻርጅ ተደርገው የሚነዱ ተሽከርካሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ገበያዎች ማቅረብ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል......
    0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • እኛ #ኢትዮጵያውያን ተቀራርበን ፣ተደማምጠን እና ተደጋግፈን መስራት በመቻላችን ልዩነት ፈጥረናል፤ባይተዋር አድርገውን የነበሩ አለም አቀፍ ስምምነቶችን መገርሰስ ችለናል፤ከሁሉ በላይ ደግሞ ፕሮጀክቱ ከድህነት ብቻ ሳይሆን ከቴክኖሎጂ ጥገኝነት ለመላቀቅ አስችሎናል!!" -#የታላቁ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ስመኘው በቀለ
    "ለልማታችን ለእድገታችን ቁልፍ መሳሪያ የሆነው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ትውልድን እያነፀ ያለ ለወደፊት የማይነቃንቅ ደፋርና በስራ የሚያምን፣ በሃገሩ ልበ ሙሉ የሆነ ወጣትን ትውልድን ማነፅ የቻለ ሆኗል"
    0 Comments 0 Shares
  • Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares