• አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ለቻን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዝግጅት ተጫዋቾችን መርጠዋል፡፡

    አሰልጣኙ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በጋና ከተሸነፈው ስብስብ መጠነኛ ለውጦች ያደረጉ ሲሆን አዳዲስ ተጫዋቾችም ጥሪ ደርሷቸዋል፡፡

    የድሬዳዋ ከተማው ሳምሶን አሰፋ ጥሪ ሲቀርብለት ዋናው ግብ ጠባቂ አቤል ማሞ ከስብስቡ ውጪ ሆኗል፡፡

    በግራ ተከላካይ መስመር የፋሲል ከነማው አምሳሉ ጥላሁን እና የሀዋሳ ከተማው አምበል ደስታ ዮሀንስ ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡

    በአንጻሩ አዲስ ተስፋዬ እና ተስፋዬ በቀለ ከጋናው ቡድን ተቀናሽ ሆነዋል፡፡

    በአማካይ ስፍራ ሽመልስ በቀለ ለጨዋታው ተገቢ ባለመሆኑ እና ጋቶች ፓኖም በቅርቡ ወደ ሩሲያ በማቅናቱ በቡድኑ አልተካተቱም፡፡

    ብሩክ ቃልቦሬም ከስብስቡ ውጪ ሲሆን፥ የቅዱስ ጊዮርጊሶቹ በኃይሉ አሰፋ፣ ናትናኤል ዘለቀ እና ምንተስኖት አዳነ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማው ታፈሰ ሰለሞን በእነርሱ ምትክ ተጠርተዋል፡፡

    የንግድ ባንኩ ቢንያም በላይ ጥሪ ቢደረግለትም ለሙከራ ወደ ጀርመን በማቅናቱ በቡድኑ ሳይካተት ቀርቷል፡፡

    በአጥቂ መስመር ኡመድ ኡኩሪ ለጨዋታው ተገቢ ባለመሆኑ ሲቀነስ ተጨማሪ ተጫዋች ቡድኑን አልተቀላቀለም፡፡

    አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ በቻን 2018 ማጣሪያ ጅቡቲን የሚገጥመው ስብስባቸውን ይዘው ወደ ድሬዳዋ ያመራሉ፡፡

    ለማጣሪያው የመተመረጡ ተጫዋቾች፤

    ግብ ጠባቂዎች

    ጀማል ጣሰው (ጅማ አባ ቡና)፣ ሳምሶን አሰፋ (ድሬዳዋ ከተማ) እና ለአለም ብርሃኑ (ሲዳማ ቡና)

    ተከላካዮች

    አስቻለው ታመነ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)፣ ሳልሃዲን በርጌቾ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)፣ አብዱልከሪም መሃመድ (ኢትዮጵያ ቡና)፣ አንተነህ ተስፋዬ (ሲዳማ ቡና)፣ ሙጂብ ቃሲም (አዳማ ከተማ)፣ ስዩም ተስፋዬ (ደደቢት)፣ ደስታ ዮሀንስ (ሀዋሳ ከተማ) እና አምሳሉ ጥላሁን (ፋሲል ከነማ)

    አማካዮች

    ሽመክት ጉግሳ (ደደቢት)፣ ሙሉአለም መስፍን (ሲዳማ ቡና)፣ ጋዲሳ መብራቴ (ሃዋሳ ከተማ)፣ ታፈሰ ሰለሞን (ሀዋሳ ከተማ) እንዲሁም ምንተስኖት አዳነ፣ ናትናኤል ዘለቀ እና በኃይሉ አሰፋ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)

    አጥቂዎች

    ጌታነህ ከበደ (ደደቢት)፣ አዲስ ግደይ (ሲዳማ ቡና)፣ አብዱልራህማን ሙባረክ (ፋሲል ከነማ) እና ሳልሃዲን ሰዒድ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ሆነው ተመርጠዋል፡፡
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ለቻን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዝግጅት ተጫዋቾችን መርጠዋል፡፡ አሰልጣኙ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በጋና ከተሸነፈው ስብስብ መጠነኛ ለውጦች ያደረጉ ሲሆን አዳዲስ ተጫዋቾችም ጥሪ ደርሷቸዋል፡፡ የድሬዳዋ ከተማው ሳምሶን አሰፋ ጥሪ ሲቀርብለት ዋናው ግብ ጠባቂ አቤል ማሞ ከስብስቡ ውጪ ሆኗል፡፡ በግራ ተከላካይ መስመር የፋሲል ከነማው አምሳሉ ጥላሁን እና የሀዋሳ ከተማው አምበል ደስታ ዮሀንስ ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡ በአንጻሩ አዲስ ተስፋዬ እና ተስፋዬ በቀለ ከጋናው ቡድን ተቀናሽ ሆነዋል፡፡ በአማካይ ስፍራ ሽመልስ በቀለ ለጨዋታው ተገቢ ባለመሆኑ እና ጋቶች ፓኖም በቅርቡ ወደ ሩሲያ በማቅናቱ በቡድኑ አልተካተቱም፡፡ ብሩክ ቃልቦሬም ከስብስቡ ውጪ ሲሆን፥ የቅዱስ ጊዮርጊሶቹ በኃይሉ አሰፋ፣ ናትናኤል ዘለቀ እና ምንተስኖት አዳነ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማው ታፈሰ ሰለሞን በእነርሱ ምትክ ተጠርተዋል፡፡ የንግድ ባንኩ ቢንያም በላይ ጥሪ ቢደረግለትም ለሙከራ ወደ ጀርመን በማቅናቱ በቡድኑ ሳይካተት ቀርቷል፡፡ በአጥቂ መስመር ኡመድ ኡኩሪ ለጨዋታው ተገቢ ባለመሆኑ ሲቀነስ ተጨማሪ ተጫዋች ቡድኑን አልተቀላቀለም፡፡ አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ በቻን 2018 ማጣሪያ ጅቡቲን የሚገጥመው ስብስባቸውን ይዘው ወደ ድሬዳዋ ያመራሉ፡፡ ለማጣሪያው የመተመረጡ ተጫዋቾች፤ ግብ ጠባቂዎች ጀማል ጣሰው (ጅማ አባ ቡና)፣ ሳምሶን አሰፋ (ድሬዳዋ ከተማ) እና ለአለም ብርሃኑ (ሲዳማ ቡና) ተከላካዮች አስቻለው ታመነ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)፣ ሳልሃዲን በርጌቾ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)፣ አብዱልከሪም መሃመድ (ኢትዮጵያ ቡና)፣ አንተነህ ተስፋዬ (ሲዳማ ቡና)፣ ሙጂብ ቃሲም (አዳማ ከተማ)፣ ስዩም ተስፋዬ (ደደቢት)፣ ደስታ ዮሀንስ (ሀዋሳ ከተማ) እና አምሳሉ ጥላሁን (ፋሲል ከነማ) አማካዮች ሽመክት ጉግሳ (ደደቢት)፣ ሙሉአለም መስፍን (ሲዳማ ቡና)፣ ጋዲሳ መብራቴ (ሃዋሳ ከተማ)፣ ታፈሰ ሰለሞን (ሀዋሳ ከተማ) እንዲሁም ምንተስኖት አዳነ፣ ናትናኤል ዘለቀ እና በኃይሉ አሰፋ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) አጥቂዎች ጌታነህ ከበደ (ደደቢት)፣ አዲስ ግደይ (ሲዳማ ቡና)፣ አብዱልራህማን ሙባረክ (ፋሲል ከነማ) እና ሳልሃዲን ሰዒድ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ሆነው ተመርጠዋል፡፡
    WWW.FANABC.COM
    FBC - አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ለቻን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ለቻን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዝግጅት ተጫዋቾችን መርጠዋል፡፡ አሰልጣኙ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በጋና ከተሸነፈው ስብስብ መጠነኛ ለውጦች ያደረ...
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ወንዶች ጥሎ ማለፍ ሁለት የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተደርገዋል።

    ለትናንት ፕሮግራም ተይዞላቸው የነበሩት አዲስ አበባ ከተማ ከጅማ አባ ቡና እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከወላይታ ዲቻ ጨዋታዎች ናቸው ዛሬ የተደረጉት።

    በሰበታ ስታዲየም ረፋድ ላይ እና ምሳ ሰዓት በተደረጉት ሁለት ጨዋታዎች፥ ጅማ አባ ቡና እና ወላይታ ዲቻ ግማሽ ፍጻሜ መግባታቸውን አረጋግጠዋል።

    ረፋድ ላይ በተደረገው ጨዋታ አዲስ አበባ ከተማ ከጅማ አባ ቡና ተጫውተዋል።

    መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ምንም ጎል ሳይቆጠርበት በአቻ ውጤት ተጠናቋል።

    አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠው የመለያ ምት ጅማ አባ ቡና 5 ለ 4 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል።

    ምሳ ሰዓት ላይ በተደረገው ሌላ ጨዋታ ደግሞ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከወላይታ ዲቻ ተገናኝተዋል።

    ጨዋታው በተመሳሳይ መልኩ ጎል ሳይቆጠርበት በአቻ ውጤት ነበር የተጠናቀቀው።

    በመለያ ምትም ወላይታ ዲቻ 4 ለ 3 በማሸነፍ አራተኛው የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል።

    መከላከያ እና ወልዲያ ከተማ ከዚህ ቀደም ግማሽ ፍጻሜውን መቀላቀል የቻሉ ቡድኖች ናቸው።

    ግማሽ ፍጻሜ ለመግባት ከተደረጉ አራት ጨዋታዎች መካከል ሶስቱ በመለያ ምት ተጠናቀዋል።

    ወልዲያ ከተማ ፋሲል ከነማን 2 ለ 0 ያሸነፈበት ጨዋታ ብቸኛው በመደበኛ ዘጠና ደቂቃ የተጠናቀቀ ጨዋታ ነው።
    አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ወንዶች ጥሎ ማለፍ ሁለት የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተደርገዋል። ለትናንት ፕሮግራም ተይዞላቸው የነበሩት አዲስ አበባ ከተማ ከጅማ አባ ቡና እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከወላይታ ዲቻ ጨዋታዎች ናቸው ዛሬ የተደረጉት። በሰበታ ስታዲየም ረፋድ ላይ እና ምሳ ሰዓት በተደረጉት ሁለት ጨዋታዎች፥ ጅማ አባ ቡና እና ወላይታ ዲቻ ግማሽ ፍጻሜ መግባታቸውን አረጋግጠዋል። ረፋድ ላይ በተደረገው ጨዋታ አዲስ አበባ ከተማ ከጅማ አባ ቡና ተጫውተዋል። መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ምንም ጎል ሳይቆጠርበት በአቻ ውጤት ተጠናቋል። አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠው የመለያ ምት ጅማ አባ ቡና 5 ለ 4 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል። ምሳ ሰዓት ላይ በተደረገው ሌላ ጨዋታ ደግሞ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከወላይታ ዲቻ ተገናኝተዋል። ጨዋታው በተመሳሳይ መልኩ ጎል ሳይቆጠርበት በአቻ ውጤት ነበር የተጠናቀቀው። በመለያ ምትም ወላይታ ዲቻ 4 ለ 3 በማሸነፍ አራተኛው የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል። መከላከያ እና ወልዲያ ከተማ ከዚህ ቀደም ግማሽ ፍጻሜውን መቀላቀል የቻሉ ቡድኖች ናቸው። ግማሽ ፍጻሜ ለመግባት ከተደረጉ አራት ጨዋታዎች መካከል ሶስቱ በመለያ ምት ተጠናቀዋል። ወልዲያ ከተማ ፋሲል ከነማን 2 ለ 0 ያሸነፈበት ጨዋታ ብቸኛው በመደበኛ ዘጠና ደቂቃ የተጠናቀቀ ጨዋታ ነው።
    WWW.FANABC.COM
    FBC - በጥሎ ማለፉ ጅማ አባ ቡና እና ወላይታ ዲቻ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅለዋል
    አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ወንዶች ጥሎ ማለፍ ሁለት የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተደርገዋል። ለትናንት ፕሮግራም ተይዞላቸው የነበሩት አዲስ አበባ ከተማ ከጅማ አባ ቡና እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከወላይታ...
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) 31ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።

    በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ የሚካሄደው የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ በተለያዩ ተጠባቂ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል።

    በስብሰባው ባለፈው የመሪዎች ጉባኤ የተላለፉ ውሳኔዎችን ተፈጻሚነት የሚገመግም ይሆናል፡፡

    ከዚህ ባለፈም የፊታችን ሰኞና ማክሰኞ ለሚካሄደው የመሪዎች ጉባኤ አጀንዳ በመቅረጽ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎም ይጠበቃል።
    አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) 31ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ የሚካሄደው የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ በተለያዩ ተጠባቂ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል። በስብሰባው ባለፈው የመሪዎች ጉባኤ የተላለፉ ውሳኔዎችን ተፈጻሚነት የሚገመግም ይሆናል፡፡ ከዚህ ባለፈም የፊታችን ሰኞና ማክሰኞ ለሚካሄደው የመሪዎች ጉባኤ አጀንዳ በመቅረጽ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎም ይጠበቃል።
    WWW.FANABC.COM
    FBC - የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ እየተካሄደ ነው
    አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) 31ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ የሚካሄደው የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ በተለያዩ ተ...
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በሻሸመኔ ሪፈራል ሆስፒታል በሕዝብ ስም በእገዛ ከውጪ የመጡ የሕክምና መሳሪያዎች ያለ አገልግሎት ከስድስት አመታት በላይ ተቀምጠዋል፡፡

    በከፍተኛ ወጪ ወደ ሆስፒታሉ የገቡ መሳሪያዎችን በተመለከተ የሻሸመኔ ፋና ኤፍ ኤም ባልደረባችን በስፍራው ባደረገው ቅኝት ያለ ምንም አገልግሎት መቀመጣቸውን ታዝቧል።

    አምቡላንስን ጨምሮ እንደ ሲ ቲ ስካን እና ማሞ ግራፊ የመሳሰሉ የሕክምና መሳሪያዎችም ያለ አገልግሎት ግቢ ውስጥ ተቀምጠዋል።

    አንድ አምቡላንስ፣ አንድ ተንቀሳቃሽ የህክምና አገልግሎት መስጫ ተሽከርካሪ እና አንድ የዳቦ መጋገሪያም ለፀሃይና ዝናብ በተጋለጠ መልኩ ተቀምጠዋል።

    መሳሪያዎቹ ያለ አገልግሎት መቀመጣቸው ደግሞ የአካባቢው ነዋሪዎች የተሻለ ህክምና ለማግኘት ወደ ሃዋሳ እና አዲስ አበባ እንዲጓዙ አድርጓቸዋል።

    ይህ መሆኑም ለተጨማሪ ወጪ እና ጊዜ እየዳረጋቸው መሆኑንም ይናገራሉ።

    የሆስፒታሉ የፋይናንስ አስተዳደር ሃላፊ አቶ ሺፈራው ቶሌራ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ምላሽ፥ ለሲ ቲ ስካንና ለማሞ ግራፊው ማስቀመጫ የሚሆን አመች ክፍል ባለመኖሩ አገልግሎቱን መስጠት እንዳልተቻለ ተናግረዋል።

    ችግሩን ለመቅረፍም ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመነጋገር ለመሳሪያዎቹ የሚመጥንና አመች የህንጻ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት።

    አምቡላንሱ እና ሌሎች የህክምና መሳሪያዎች በመለዋወጫ እጥረት ሳቢያ አገልግሎት መስጠት አለመቻላቸውንም አንስተዋል።

    የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ ፈይሳ ሳፈው በበኩላቸው፥ ለመሳሪያዎቹ የሚመጥን ክፍል እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው አጠቃላይ ችግሩን ለመቅረፍ እየተሰራ ነው ብለዋል።

    ከዚህ ጋር ተያይዞም ለዳቦ መጋገሪያው ስራ አለመጀመር ምክንያት የሆነውን የመብራት አገልግሎት ችግር ለመቅረፍ ትራንስፎርመር እየተተከለ መሆኑን ጠቅሰዋል።

    ለተሽከርካሪዎቹ የሚሆን መለዋወጫ በማቅረብም ወደ ስራ እንዲገቡ ይደረጋልም ነው ያሉት፤ አጠቃላይ ችግሩ ተፈቶ በቀጣዩ አመት መሳሪያዎቹ ወደ አገልግሎት እንደሚገቡም አስረድተዋል።
    አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በሻሸመኔ ሪፈራል ሆስፒታል በሕዝብ ስም በእገዛ ከውጪ የመጡ የሕክምና መሳሪያዎች ያለ አገልግሎት ከስድስት አመታት በላይ ተቀምጠዋል፡፡ በከፍተኛ ወጪ ወደ ሆስፒታሉ የገቡ መሳሪያዎችን በተመለከተ የሻሸመኔ ፋና ኤፍ ኤም ባልደረባችን በስፍራው ባደረገው ቅኝት ያለ ምንም አገልግሎት መቀመጣቸውን ታዝቧል። አምቡላንስን ጨምሮ እንደ ሲ ቲ ስካን እና ማሞ ግራፊ የመሳሰሉ የሕክምና መሳሪያዎችም ያለ አገልግሎት ግቢ ውስጥ ተቀምጠዋል። አንድ አምቡላንስ፣ አንድ ተንቀሳቃሽ የህክምና አገልግሎት መስጫ ተሽከርካሪ እና አንድ የዳቦ መጋገሪያም ለፀሃይና ዝናብ በተጋለጠ መልኩ ተቀምጠዋል። መሳሪያዎቹ ያለ አገልግሎት መቀመጣቸው ደግሞ የአካባቢው ነዋሪዎች የተሻለ ህክምና ለማግኘት ወደ ሃዋሳ እና አዲስ አበባ እንዲጓዙ አድርጓቸዋል። ይህ መሆኑም ለተጨማሪ ወጪ እና ጊዜ እየዳረጋቸው መሆኑንም ይናገራሉ። የሆስፒታሉ የፋይናንስ አስተዳደር ሃላፊ አቶ ሺፈራው ቶሌራ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ምላሽ፥ ለሲ ቲ ስካንና ለማሞ ግራፊው ማስቀመጫ የሚሆን አመች ክፍል ባለመኖሩ አገልግሎቱን መስጠት እንዳልተቻለ ተናግረዋል። ችግሩን ለመቅረፍም ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመነጋገር ለመሳሪያዎቹ የሚመጥንና አመች የህንጻ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑንም ነው የተናገሩት። አምቡላንሱ እና ሌሎች የህክምና መሳሪያዎች በመለዋወጫ እጥረት ሳቢያ አገልግሎት መስጠት አለመቻላቸውንም አንስተዋል። የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ ፈይሳ ሳፈው በበኩላቸው፥ ለመሳሪያዎቹ የሚመጥን ክፍል እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው አጠቃላይ ችግሩን ለመቅረፍ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከዚህ ጋር ተያይዞም ለዳቦ መጋገሪያው ስራ አለመጀመር ምክንያት የሆነውን የመብራት አገልግሎት ችግር ለመቅረፍ ትራንስፎርመር እየተተከለ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለተሽከርካሪዎቹ የሚሆን መለዋወጫ በማቅረብም ወደ ስራ እንዲገቡ ይደረጋልም ነው ያሉት፤ አጠቃላይ ችግሩ ተፈቶ በቀጣዩ አመት መሳሪያዎቹ ወደ አገልግሎት እንደሚገቡም አስረድተዋል።
    WWW.FANABC.COM
    FBC - በሻሸመኔ ሪፈራል ሆስፒታል የሕክምና መሳሪያዎች ያለ አገልግሎት ከስድስት አመታት በላይ ተቀምጠዋል
    አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በሻሸመኔ ሪፈራል ሆስፒታል በሕዝብ ስም በእገዛ ከውጪ የመጡ የሕክምና መሳሪያዎች ያለ አገልግሎት ከስድስት አመታት በላይ ተቀምጠዋል፡፡ በከፍተኛ ወጪ ወደ ሆስፒታሉ የገቡ መሳሪያዎችን በተመ...
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ ቅጥቅጥ አይሱዙ መለስተኛ የህዘብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተገልብጦ 16 ሰዎች ሞቱ።

    ተሽከርካሪው ዛሬ በኦሮሚያ ከልል ምዕራብ ሃረርጌ ዞን ጭሮ ከተማ አቅራቢያ ሲደርስ ነው የተገለበጠው።

    በወቅቱ 25 ሰዎች መጫን ቢገባውም 40 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ ነበር ተብሏል።

    በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በጭሮ እና አዳማ ሆስፒታሎች የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ሲሆን፥ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ ወደ አዲስ አበባ ተልከዋል።

    የምዕራብ ሃረርጌ ዞን ፖሊስ ፅህፈት ቤት፥ ተሽከርካሪው ከልክ በላይ መጫኑን ጠቅሶ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን አስታውቋል።

    በሳምንቱ በክልሉ በትራፊክ አደጋ ሳቢያ ከ88 በላይ ሰዎች ህይዎት አልፏል።

    በክልሉ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለውን የትራፊክ አደጋ ለመቆጣጠር፥ የክልሉ ትራንስፖርት ባለስልጣን ወደ እርምጃ መግባቱን አስታውቋል።

    የባለስልጣኑ ሃላፊ አቶ ታከለ ኡማ እንዳሉት፥ ከዚህ ጋር ተያይዞ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው።

    የህዝብ ትራንስፖርት በሌሊት እንዳይሰጥ ማድረግ፣ ስምሪቱን በአዲስ መልክ የማደራጀት፣ የትራፊክ አደጋ የሚበዛባቸው 270 አካባቢዎች ላይ ጥናት ማድረግም እየተተገበሩ ያሉ እርምጃዎች ናቸው ብለዋል።

    ይህን ለማስፈጸምም ባለስልጣኑ ከትራፊክ ተቆጣጣሪዎች፣ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ፍትህ ቢሮ፣ ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ፣ መንገዶች ባለስልጣን እና ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ በቅንጅት እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
    አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ ቅጥቅጥ አይሱዙ መለስተኛ የህዘብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተገልብጦ 16 ሰዎች ሞቱ። ተሽከርካሪው ዛሬ በኦሮሚያ ከልል ምዕራብ ሃረርጌ ዞን ጭሮ ከተማ አቅራቢያ ሲደርስ ነው የተገለበጠው። በወቅቱ 25 ሰዎች መጫን ቢገባውም 40 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ ነበር ተብሏል። በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በጭሮ እና አዳማ ሆስፒታሎች የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ሲሆን፥ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ ወደ አዲስ አበባ ተልከዋል። የምዕራብ ሃረርጌ ዞን ፖሊስ ፅህፈት ቤት፥ ተሽከርካሪው ከልክ በላይ መጫኑን ጠቅሶ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን አስታውቋል። በሳምንቱ በክልሉ በትራፊክ አደጋ ሳቢያ ከ88 በላይ ሰዎች ህይዎት አልፏል። በክልሉ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለውን የትራፊክ አደጋ ለመቆጣጠር፥ የክልሉ ትራንስፖርት ባለስልጣን ወደ እርምጃ መግባቱን አስታውቋል። የባለስልጣኑ ሃላፊ አቶ ታከለ ኡማ እንዳሉት፥ ከዚህ ጋር ተያይዞ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው። የህዝብ ትራንስፖርት በሌሊት እንዳይሰጥ ማድረግ፣ ስምሪቱን በአዲስ መልክ የማደራጀት፣ የትራፊክ አደጋ የሚበዛባቸው 270 አካባቢዎች ላይ ጥናት ማድረግም እየተተገበሩ ያሉ እርምጃዎች ናቸው ብለዋል። ይህን ለማስፈጸምም ባለስልጣኑ ከትራፊክ ተቆጣጣሪዎች፣ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ፍትህ ቢሮ፣ ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ፣ መንገዶች ባለስልጣን እና ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ በቅንጅት እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
    WWW.FANABC.COM
    FBC - ከጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ የህዘብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተገልብጦ 16 ሰዎች ሞቱ
    አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ ቅጥቅጥ አይሱዙ መለስተኛ የህዘብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተገልብጦ 16 ሰዎች ሞቱ። ተሽከርካሪው ዛሬ በኦሮሚያ ከልል ምዕራብ ሃረ...
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩስያ አቻቸው ጋር በቀጣዩ ሳምንት በጀርመን እንደሚወያዩ ዋይት ሀውስ አረጋገጠ።

    የአሜሪካ ብሄራዊ የደህንነት አማካሪ ሀርበርት ሬሞንድ ማክማስተር እንደተናገሩት፥ ሁለቱ መሪዎች ከቡድን 20 አባል ሀገራት ጉባኤ ጎን ለጎን ነው በሀምቡርግ የሚመክሩት።

    የህብረቱ አባል ሀገራት ጉባኤ ከሰኔ 30 እስከ ሀምሌ 1 2009 ይደረጋል።

    ፕሬዚዳንት ፑቲን ከዚህ ቀደም ግልፅ እንዳደረጉት ሩስያ ከአሜሪካም ሆነ ከምዕራቡ አለም ጋር ያላት ግንኙነት እንዲሻሻል ትፈልጋለች ነው ያሉት አማካሪው።

    በመሪዎቹ ውይይት ሩስያ በ2016ቱ የአሜሪካ ምርጫ ጣልቃ ገብተሻል በሚል የቀረበባትን ወቀሳ አስመልክቶ ሊመክሩ እንደሚችሉ ግን ያሉት ነገር የለም።

    የትራምፕ አስተዳደር ከሩስያ እና የተወሰኑ አማካሪዎቻቸው ከሞስኮ ጋር ያላቸው ግንኙነት በ2016ቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ላይ ተፅዕኖ ፈጥሯል በሚል መነጋገሪያ መሆኑ ይታወሳል።

    በምርጫው የሞስኮ ተሳትፎ ስለመኖሩም የማጣራት ስራው ቀጥሏል።

    ትራምፕ በተለያዩ አጋጣሚዎች አሜሪካ ከሩስያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማሳደግ እንደምትሰራ መግለፃቸው ይታወሳል።

    ፑቲን በበኩላቸው የሞስኮ እና ዋሽንግተን ግንኙነት ወደነበረበት መመለስ የሁለቱንም ወገኖች ጥቅም እንደሚያስጠብቅ መናገራቸው አይዘነጋም።

    አሜሪካ እና ሩስያ በሶሪያ እና ዩክሬን ግጭት ጨምሮ በሌሎች ሀገራት ዙሪያ በሚከተሏቸው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ዙሪያ ሲወዛገቡ ይታያል።

    ዋሽንግተን እና አጋሮቿ የምስራቃዊ ዩክሬን አፍቃሪ ሩስያ ሀይሎችን ደግፋለች በሚል በሞስኮ ላይ ሰፊ የኢኮኖሚ ማዕቀብ መጣሏ ይታወቃል።

    ምንጭ፦ ፕሬስ ቲቪ
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩስያ አቻቸው ጋር በቀጣዩ ሳምንት በጀርመን እንደሚወያዩ ዋይት ሀውስ አረጋገጠ። የአሜሪካ ብሄራዊ የደህንነት አማካሪ ሀርበርት ሬሞንድ ማክማስተር እንደተናገሩት፥ ሁለቱ መሪዎች ከቡድን 20 አባል ሀገራት ጉባኤ ጎን ለጎን ነው በሀምቡርግ የሚመክሩት። የህብረቱ አባል ሀገራት ጉባኤ ከሰኔ 30 እስከ ሀምሌ 1 2009 ይደረጋል። ፕሬዚዳንት ፑቲን ከዚህ ቀደም ግልፅ እንዳደረጉት ሩስያ ከአሜሪካም ሆነ ከምዕራቡ አለም ጋር ያላት ግንኙነት እንዲሻሻል ትፈልጋለች ነው ያሉት አማካሪው። በመሪዎቹ ውይይት ሩስያ በ2016ቱ የአሜሪካ ምርጫ ጣልቃ ገብተሻል በሚል የቀረበባትን ወቀሳ አስመልክቶ ሊመክሩ እንደሚችሉ ግን ያሉት ነገር የለም። የትራምፕ አስተዳደር ከሩስያ እና የተወሰኑ አማካሪዎቻቸው ከሞስኮ ጋር ያላቸው ግንኙነት በ2016ቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ላይ ተፅዕኖ ፈጥሯል በሚል መነጋገሪያ መሆኑ ይታወሳል። በምርጫው የሞስኮ ተሳትፎ ስለመኖሩም የማጣራት ስራው ቀጥሏል። ትራምፕ በተለያዩ አጋጣሚዎች አሜሪካ ከሩስያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማሳደግ እንደምትሰራ መግለፃቸው ይታወሳል። ፑቲን በበኩላቸው የሞስኮ እና ዋሽንግተን ግንኙነት ወደነበረበት መመለስ የሁለቱንም ወገኖች ጥቅም እንደሚያስጠብቅ መናገራቸው አይዘነጋም። አሜሪካ እና ሩስያ በሶሪያ እና ዩክሬን ግጭት ጨምሮ በሌሎች ሀገራት ዙሪያ በሚከተሏቸው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ዙሪያ ሲወዛገቡ ይታያል። ዋሽንግተን እና አጋሮቿ የምስራቃዊ ዩክሬን አፍቃሪ ሩስያ ሀይሎችን ደግፋለች በሚል በሞስኮ ላይ ሰፊ የኢኮኖሚ ማዕቀብ መጣሏ ይታወቃል። ምንጭ፦ ፕሬስ ቲቪ
    WWW.FANABC.COM
    FBC - ትራምፕ እና ፑቲን በቀጣዩ ሳምንት በጀርመን ይመክራሉ
    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2009 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩስያ አቻቸው ጋር በቀጣዩ ሳምንት በጀርመን እንደሚወያዩ ዋይት ሀውስ አረጋገጠ። የአሜሪካ ብሄራዊ የደህንነት አማካሪ ሀርበርት ሬሞንድ ማክማስተር እንደ...
    0 Comments 0 Shares
  • Hinom - Overexposed — with Opha Manhisho, Adry Joles Wahab, Pendo Maswabe and Hinom Gete.
    Hinom - Overexposed — with Opha Manhisho, Adry Joles Wahab, Pendo Maswabe and Hinom Gete.
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • Amleset and Pearls - Calendar Photoshoot project
    Makeup: Marzel Makeup Studio Marzel Alemayehu
    Headscarf: Enku Design Enkutatash Kibret
    Amleset and Pearls - Calendar Photoshoot project Makeup: Marzel Makeup Studio Marzel Alemayehu Headscarf: Enku Design Enkutatash Kibret
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares