• Like
    2
    0 Comments 0 Shares
  • የሜርኩሪ ማእድን አለን በማለት ከ9 ሚልየን ብር በላይ አንድን ግለሰብ በማጭበርበር ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በተባሉ አራት ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ።

    ተከሳሾቹ ሬድዋን ሀሩን፣ እስክንድር ሰይድ፣ ሪዳ አሊ እና መሀመድ ቃይድ የሚባሉ ናቸው።

    1ኛ፣ 2ኛ እና 4ኛ ተከሳሾች ነዋሪነታቸው በድሬዳዋ ከተማ እና በአዲስ አበባ ሲሆን፥ 3ኛ ተከሳሽ ግን በዜግነት ጅቡቲያዊ ናቸው።

    የከሳሽ አቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር እንደሚያስረዳው፥ ግለሰቦቹ የማይገባቸውን ብልፅግና ለማግኘት በማሰብ ቢላል የተባለን ግለሰብ የአቃቤ ህግ ሶስተኛ ምስክር የሆነ መስፍን የተባለ ግለሰብ እንዲያስተዋውቃቸው ያደርጉታል።

    ከዚያም “የሜርኩሪው ባለቤቶች ድሬዳዋ ናቸው፤ ነገር ግን ሜርኩሪውን ለአረቦች ሊሸጡት ስለሆነ አንተ የገንዘብ አቅም ስላለህ ገዝተህ ተጠቀም” በማለት የግል ተበዳይን ያሳምኑታል።

    በመሆኑም በአቃቤ ህግ የክስ መዝገብ 1ኛ ተከሳሽ ሬድዋን ሀሩንና ሙክታር መሀመድ የተባለ ግለሰብ ከድሬዳዋ የመጡ ግለሰቦች መስለው የግል ተበዳይን ይተዋወቁታል።

    ታህሳስ 21 ቀን 2008 ዓ.ም ከግል ተበዳይ መኖርያ ቤት በመሄድ ሜርኩሪውን እንፈትሸው በማለት ሙክታር መሀመድ የተባለው ግለሰብ ሜርኩሪ የተባለውን ቁስ ከጣቱ ቀለበት ጋር አንድ ላይ በመያዝ እና የተለያዩ ድምጾችን ጮክ ብሎ በማሰማት ሜርኩሪው ሰርቷል በማለት ጨብጠዋቸዋል ነው የተባለው።

    ሙክታር የተባለው ግለሰብ፥ ከዚህ በኋላ ስራውን ከአረቦቹ ጋር ጨርስ በማለት ከቤቱ የወጣ ሲሆን፥ የግል ተባዳይም ባዩት ነገር ተስማምተው 500 ሺህ ብር ከባንክ አውጥተው ለ1ኛ ተከሳሽ እና መሀመድ አብደላ ለተባለ ግለሰብ እንደሰጧቸውም በክሱ ተጠቅሷል።

    ግለሰቦቹ ገንዘቡን ከወሰዱ በኋላም በድጋሜ መጋቢት ወር 2008 ዓ.ም ሜርኩሪውን የሚገዛው አረብ ብሩን የሚልክልህ ባንተ ስም ስለሆነ ከሱ ላይ የሚቀነስ 4 ነጥብ 5 ሚልየን ብር ስጠን በማለት 1ኛ እና 4ኛ ተከሳሾች ገንዘቡን ከግል ተበዳዩ ግለሰብ ወስደዋል።

    በዚህ ያላበቁት ግለሰቦቹ ከወራቶች ቆይታ በኋላ የጠፋነው አረብ አገር ለስራ ሄደን ነበር በማለት 1ኛ ተከሳሽ ስሙን በመቀየር ዶክተር ሪያድ በማለይ ግለሰቡን ከተዋወቀው በኋላ በስራ ጉዳይ አውርተዋል።

    1ኛ ተከሳሽ ግለሰቡን ጅቡቲ ወደብ ላይ የውሃ መቆፈሪያ ማሽኖች አሉኝ በማለት ካሳመነው በኋላ፥ አንተ ሱሉልታ ለውሃ ምርት የሚሆን መሬት ፈልግ በማለት እንደተናገረው አቃቤ ህግ በክሱ አብራርቶታል።

    ማሽኖቹንም ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት በሚል የ700 ሺህ ብር ቼክ እና 1 ነጥብ 2 ሚልየን ብር በአጠቃላይ ከ9 ሚልየን ብር በላይ ከግለሰቡ በማታለል ወስደዋል ነው ያለው አቃቤ ህግ በክሱ።

    ከሳሽ አቃቤ ህግም ግለሰቦቹ በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት የማታለል ወንጀል ክስ መስርቶባቸዋል።

    ተከሳሾቹም ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 8ኛው የወንጀል ችሎት የዋስትና ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን፥ አቃቤ ህግም ከወንጀሉ ክብደት እና 3ኛ ተከሳሽ የውጭ ዜግነት ያላቸው በመሆኑ በዋስትና ቢለቀቁ ላይቀርቡ ይችላሉ በማለት ዋስትናውን ተቃውሟል።

    ፍርድ ቤቱም በዋስትናው ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ለከሰዓት ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።

    Like
    2
    0 Comments 0 Shares
  • በአማራ እና ትግራይ ክልሎች በተያዘው ዓመት በጥናት በተለዩ 45 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ላይ የከርሰ ምድር ውሃ መገኛ አከባቢያዊ ካርታ ሊዘጋጅ መሆኑን የእርሻ እና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስቴር አስታወቀ።

    ሚኒስቴሩ ዘንድሮ በጥናት በለያቸው በሁለቱ ክልሎች የመስኖ ከርሰ ምድር ውሃ፥ አርሶ አደሩን በመስኖ ልማት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው ተብሏል።

    በሚኒስቴሩ አነስተኛ መስኖ ልማት ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ አወል ለፋና ብሮድካስቲግ ኮርፖርት እንደተናገሩት፥ ሚኒስቴሩ የከርሰ ምድር ውሃ መገኛ አካባቢያዊ ካርታ ያዘጋጃል።

    በ2010 ዓ.ም የተጠናቀቀው ይህ ጥናት፥ አቶ ኤልያስ በሁለቱ ክልሎች በ45 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ውስጥ የከርሰ ምድር ውሃ 85 በመቶ መኖሩን አረጋግጧል ብለዋል።

    በዚህ መልኩ የተለዩትን ቦታዎች ካርታ ከማዘጋጀት ጎን ለጎን በቁፋሮ ዘርፍ ስራ ፈላጊ ወጣቶችን በማሰማራት ከየካቲት ወር ጀምሮ የቁፋሮ ስራ ይጀመራል ነው የተባለው።

    ቁፋሮው ሲጠናቀቅ አርሶ አደሩ በሚወጣው የከርሰ ምድር ውሃ በመስኖ ልማቱ ተጠቃሚ እንደሚሆን ተገልጿል።
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • https://www.esetube.com/ethiopian-bank-insurance-job-vacancy/
    Ethiopian Bank Insurance Job Vacancy
    Like
    1
    0 Comments 0 Shares
  • https://www.esetube.com/ethiopian-bank-insurance-job-vacancy/
    Ethiopian Bank Insurance Job Vacancy
    0 Comments 0 Shares
  • የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚያም ሊገነባ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚስቴር ተናገረ
    የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚያም ሊገነባ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚስቴር ተናገረ፡፡ሚንስትሯ ዶ/ር ሒሩት ወ/ማርያም የመስሪያ ቤታቸውን የግማሽ አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ለሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ሲያቀርቡ እንዳሉት የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚገነባው በአድዋ ከተማ ነው፡፡

    ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ጋር በመተባበር የሙዚየሙን የግንባታ ፕሮጀክት መነሻ ጥናት አጠናቋል ተብሏል፡፡የአድዋ ከተማ አስተዳደር ለአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚሆን ቦታ ማዘጋጀቱን ሰምተናል፡፡

    ለግንባታው በአሜሪካ የሚገኙ የተለያዩ ተቋማት አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርጉልን ቃል ገብተዋል ብለዋል ሚኒስትሯ፡፡በተያያዘ ከ13 አመት በፊት ከሮም የተመለሰውን እና በብረት ድጋፍ የቆመውን ቁጥር ሶስት የአክሱም ሐውልት የብረት ድጋፉን አንስቶ ለሐውልቶቹ ዘላቂ የመሰረት ጥገና ለማድረግ ከጣሊያን ድርጅት ጋር ውል መፈረሙን ሰምተናል፡፡

    የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ እንዳሉት ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገባባቸውና የአለም ቅርስ ከሆኑ መካከል የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ሲሆን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች ገጥመውታል፡፡መላ ለመፈለግም በኢትዮጵያ በቅርስ ጥገና ላይ የተሻለ እውቀት ያላቸው ምሁራን እንዲያጠኑት ተደርጓል ብለዋል፡፡

    ቅርሱን ለመታደግ በመጪው ጊዜ ስለሚወሰዱ እርምጃዎች የዩኔስኮ ፍቃድና ድጋፍ ለማረጋገጥ የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል ያሉት ሚንስትሯ በጀመርነው የጥር ወር አጋማሽ ከዩኔስኮ፣ አይኮምስ እና ኢክሮም ጥምር የቴክኒክ ኮሚቴ በላሊበላ በአካል ተገኝተው ስለ ጉዳዩ ለመምከር ቀጠሮ ተይዟል፡፡

    የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመጠገን ሰማንያ ሚሊየን ዶላር ያስፈልጋል፡፡ ኢትዮጵያ የበርካታ ቅርሶች ባለቤት ብትሆንም ብዙዎቹ እርጅና ተጭኗቸው የመፍረስ አደጋ እያንዣበበባቸው ነው ተብሏል፡፡

    አገሪቱ እነዚህን ቅርሶች የሚጠግን የሰው ሀይል አለማፍራቷና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚመደበው በጀት ቅርሶቹን ለመጠገን በቂ አለመሆኑ ፈተና ሆኖብናል ብለዋል ዶ/ር ሒሩት፡፡የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ ባለው የሶስተኛ አመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የኤሌክትሮኒክስ ፊርማን ለመደንገግ እንዲሁም የህግ ምርምርና ስልጠና ኢንስቲትዩን ለማቋቋም የቀረቡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚያም ሊገነባ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚስቴር ተናገረ
    የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚያም ሊገነባ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚስቴር ተናገረ፡፡ሚንስትሯ ዶ/ር ሒሩት ወ/ማርያም የመስሪያ ቤታቸውን የግማሽ አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ለሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ሲያቀርቡ እንዳሉት የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚገነባው በአድዋ ከተማ ነው፡፡

    ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ጋር በመተባበር የሙዚየሙን የግንባታ ፕሮጀክት መነሻ ጥናት አጠናቋል ተብሏል፡፡የአድዋ ከተማ አስተዳደር ለአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚሆን ቦታ ማዘጋጀቱን ሰምተናል፡፡

    ለግንባታው በአሜሪካ የሚገኙ የተለያዩ ተቋማት አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርጉልን ቃል ገብተዋል ብለዋል ሚኒስትሯ፡፡በተያያዘ ከ13 አመት በፊት ከሮም የተመለሰውን እና በብረት ድጋፍ የቆመውን ቁጥር ሶስት የአክሱም ሐውልት የብረት ድጋፉን አንስቶ ለሐውልቶቹ ዘላቂ የመሰረት ጥገና ለማድረግ ከጣሊያን ድርጅት ጋር ውል መፈረሙን ሰምተናል፡፡

    የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ እንዳሉት ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገባባቸውና የአለም ቅርስ ከሆኑ መካከል የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱ ሲሆን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች ገጥመውታል፡፡መላ ለመፈለግም በኢትዮጵያ በቅርስ ጥገና ላይ የተሻለ እውቀት ያላቸው ምሁራን እንዲያጠኑት ተደርጓል ብለዋል፡፡

    ቅርሱን ለመታደግ በመጪው ጊዜ ስለሚወሰዱ እርምጃዎች የዩኔስኮ ፍቃድና ድጋፍ ለማረጋገጥ የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል ያሉት ሚንስትሯ በጀመርነው የጥር ወር አጋማሽ ከዩኔስኮ፣ አይኮምስ እና ኢክሮም ጥምር የቴክኒክ ኮሚቴ በላሊበላ በአካል ተገኝተው ስለ ጉዳዩ ለመምከር ቀጠሮ ተይዟል፡፡

    የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመጠገን ሰማንያ ሚሊየን ዶላር ያስፈልጋል፡፡ ኢትዮጵያ የበርካታ ቅርሶች ባለቤት ብትሆንም ብዙዎቹ እርጅና ተጭኗቸው የመፍረስ አደጋ እያንዣበበባቸው ነው ተብሏል፡፡

    አገሪቱ እነዚህን ቅርሶች የሚጠግን የሰው ሀይል አለማፍራቷና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚመደበው በጀት ቅርሶቹን ለመጠገን በቂ አለመሆኑ ፈተና ሆኖብናል ብለዋል ዶ/ር ሒሩት፡፡የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ ባለው የሶስተኛ አመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የኤሌክትሮኒክስ ፊርማን ለመደንገግ እንዲሁም የህግ ምርምርና ስልጠና ኢንስቲትዩን ለማቋቋም የቀረቡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
    0 Comments 0 Shares