ያለፉት የኢትዮጵያ ነገስታት ማዕረግ ለምን "ዘእምነገደ ይሁዳ..." የሚለውን ተቀጽላ ያዘ?
ከኢትዮያዊው ንጉስ ተዋስያንና ከእናቷ ከእቴጌ ኤስሜኒ የተወለደችው ንግስተ ሳባ ተብላ የምትታወቀው የኢትዮጵያ ንግስት ከክርስቶስ ልደት በፊት1013 ዓመት (በ3,987 ዓመተ ዓለም) ላይ የነገሰች ናት። ስሟም ገንኖ የሚታወቅበት ምክንያት ንጉስ ሰለሞን የእስራኤል ንጉስ በነበረበት ዘመን ዝናውን ሰምታ ታምሪን በሚባለው ኢትዮጵያዊ ነጋዴ አማካኝነት ልትጎበኘው በመሄዷና ከተመለሰችም በሇላ ከንጉስ ሰለሞን እብነ እልኪም የተባለውን ልጇን ስለወለደለችለት ነው።
ንግስተ ሳባ ለ31 አመት ኢትዮጵያን ስታስተዳድር ከቆየች በሇላ መንግስቷን ከክርስቶስ ልደት በፊት በ982 አመት ለዚሁ ከንጉስ ሰለሞን ለተወለደው ልጇ ለእብነ እልኪም አውርሳ ቀዳማዊ ምኒልክ ወይም ዳዊት ተብሎ ነገሰ። ነግስተ ሳባ ከመልቀቇ በፊት የንግስና ስርዓት አውጥታለች። ስርአቱም "የኢትዮጵያን ዘውድ ጭኖ በትረ መንግስት ጨብጦ መግዛት ያለበት ከቀዳማዊ ምኒልክ ዘር የተወለደ እንዲሆን፣ መንግስትም ከእሱ ዘር እንዳይዎጣ" ብላ ከማስወሰኗም በላይ ከንግስተ ሳባ (ንግስት ማክዳ ወይም አዜብ) በሇላ "ከወንዱ ወገን እንጂ ከሴት ወገን የቀዳማዊ ምኒልክን ሥርወ መንግስት ዘውድ እንዳይጨብጥ" ስትል በህግ እንዲከለክል አደረገች።
ይህን ህግ የተከተለው የአነጋገስ ስርዐት ግን እየደከመ ሄዶ በ842 ዓ.ም ዮዲት የምትባል ንግስት ነግሳ ጭራሹኑ አጠፋችው። ቀጣዩ አልጋ ወራሽም ወደ ሸዋ ሸሸ። የቀሩት የቀዳማዊ ምኒልክ ተወላጆች ንጉሱን እንዳይቀናቀኑ በወቅቱ ደብረ ዳሞ መታገት ልማድ ስለነበረ እዚያው እንዳሉ በሙል ፈጀቻቸው።
ከዮዲት ዘመነ መንግስት በሇላ ግን በ882 ዓ.ም አንበሳ ውድም ከሸዋ ተመልሶ የአክሱምን መንግስት እንደገና ለሃያ አመት ዓጸና። ሆኖም ግን በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ትግሎች የንግስተ ሳባን ህግ በመጣስ ከምኒልክ ተወላጅ ያልሆኑ መሪዎች ስልጣኑን ሲይዙ ቆዩ። ቀረብ ባሉት ጊዜያትም አፄ ቴዎድሮስ እና ዓጼ ዮሐንስ ይህን ህግ ሳይከተሉ ስልጣኑን ከያዙት መሪዎች ውስጥ ይካተታሉ።
ዳግማዊ ምኒልክ ከአፄ ዮሐንሥ ህልፈተ ሕይወት በሇላ በ1882 ዓ.ም "ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ ዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ" ብለው በማዎጅ በቅርብ ከምኒልክ የዘር ሀረግ ወጥቶ የነበረውን የንግስና ማእረግ እንደገና መለሱ። ከአፄ ምኒልክ ቀጥሎ በዚሁ ተቀፅላ የነገሡት ንግሥተ ነገሥት ዘውዲቱ ፣ በሇላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ነበሩ። ከንጉሥ ሰሎሞንና ከንግስተ ሳባ ልጅ ከቀዳማዊ ምኒልክ አንስቶ ሲቆጠር ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ 225ኛ ንጉስ ናቸው።
ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ የሚለውን ተቀፅላ ንጉሶቹ ያወጁበት ማክንያት የይሁዳ ዘር የንጉስ ዳዊት ትውልድ ነን በማለት በሕዝብና በቀሳውስት ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኙ ስለሚፈልጉ እንደሆነ ይነገራል። በዚህም አይነት ሁኔታ ያለ ንጉስ ሲነግስ ከቀዳማዊ ምኒልክ ዘር ውጪ የሚመጣን ተወዳዳሪ ቅስም ከመስበሩም በላይ በሰፊው የክርስትና ተከታይ ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ስለሚያገኝ እንደሆነ ይነገራል። በቀደሙ ጊዜያትም በዚህ ተቀፅላ ራሱን የገለፀው አፄ ኢያሱ አድያም ሰገድ ብቻ እንደነበር ታሪክ ያስረዳል ።
ከኢትዮያዊው ንጉስ ተዋስያንና ከእናቷ ከእቴጌ ኤስሜኒ የተወለደችው ንግስተ ሳባ ተብላ የምትታወቀው የኢትዮጵያ ንግስት ከክርስቶስ ልደት በፊት1013 ዓመት (በ3,987 ዓመተ ዓለም) ላይ የነገሰች ናት። ስሟም ገንኖ የሚታወቅበት ምክንያት ንጉስ ሰለሞን የእስራኤል ንጉስ በነበረበት ዘመን ዝናውን ሰምታ ታምሪን በሚባለው ኢትዮጵያዊ ነጋዴ አማካኝነት ልትጎበኘው በመሄዷና ከተመለሰችም በሇላ ከንጉስ ሰለሞን እብነ እልኪም የተባለውን ልጇን ስለወለደለችለት ነው።
ንግስተ ሳባ ለ31 አመት ኢትዮጵያን ስታስተዳድር ከቆየች በሇላ መንግስቷን ከክርስቶስ ልደት በፊት በ982 አመት ለዚሁ ከንጉስ ሰለሞን ለተወለደው ልጇ ለእብነ እልኪም አውርሳ ቀዳማዊ ምኒልክ ወይም ዳዊት ተብሎ ነገሰ። ነግስተ ሳባ ከመልቀቇ በፊት የንግስና ስርዓት አውጥታለች። ስርአቱም "የኢትዮጵያን ዘውድ ጭኖ በትረ መንግስት ጨብጦ መግዛት ያለበት ከቀዳማዊ ምኒልክ ዘር የተወለደ እንዲሆን፣ መንግስትም ከእሱ ዘር እንዳይዎጣ" ብላ ከማስወሰኗም በላይ ከንግስተ ሳባ (ንግስት ማክዳ ወይም አዜብ) በሇላ "ከወንዱ ወገን እንጂ ከሴት ወገን የቀዳማዊ ምኒልክን ሥርወ መንግስት ዘውድ እንዳይጨብጥ" ስትል በህግ እንዲከለክል አደረገች።
ይህን ህግ የተከተለው የአነጋገስ ስርዐት ግን እየደከመ ሄዶ በ842 ዓ.ም ዮዲት የምትባል ንግስት ነግሳ ጭራሹኑ አጠፋችው። ቀጣዩ አልጋ ወራሽም ወደ ሸዋ ሸሸ። የቀሩት የቀዳማዊ ምኒልክ ተወላጆች ንጉሱን እንዳይቀናቀኑ በወቅቱ ደብረ ዳሞ መታገት ልማድ ስለነበረ እዚያው እንዳሉ በሙል ፈጀቻቸው።
ከዮዲት ዘመነ መንግስት በሇላ ግን በ882 ዓ.ም አንበሳ ውድም ከሸዋ ተመልሶ የአክሱምን መንግስት እንደገና ለሃያ አመት ዓጸና። ሆኖም ግን በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ትግሎች የንግስተ ሳባን ህግ በመጣስ ከምኒልክ ተወላጅ ያልሆኑ መሪዎች ስልጣኑን ሲይዙ ቆዩ። ቀረብ ባሉት ጊዜያትም አፄ ቴዎድሮስ እና ዓጼ ዮሐንስ ይህን ህግ ሳይከተሉ ስልጣኑን ከያዙት መሪዎች ውስጥ ይካተታሉ።
ዳግማዊ ምኒልክ ከአፄ ዮሐንሥ ህልፈተ ሕይወት በሇላ በ1882 ዓ.ም "ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ ዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ" ብለው በማዎጅ በቅርብ ከምኒልክ የዘር ሀረግ ወጥቶ የነበረውን የንግስና ማእረግ እንደገና መለሱ። ከአፄ ምኒልክ ቀጥሎ በዚሁ ተቀፅላ የነገሡት ንግሥተ ነገሥት ዘውዲቱ ፣ በሇላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ነበሩ። ከንጉሥ ሰሎሞንና ከንግስተ ሳባ ልጅ ከቀዳማዊ ምኒልክ አንስቶ ሲቆጠር ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ 225ኛ ንጉስ ናቸው።
ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ የሚለውን ተቀፅላ ንጉሶቹ ያወጁበት ማክንያት የይሁዳ ዘር የንጉስ ዳዊት ትውልድ ነን በማለት በሕዝብና በቀሳውስት ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኙ ስለሚፈልጉ እንደሆነ ይነገራል። በዚህም አይነት ሁኔታ ያለ ንጉስ ሲነግስ ከቀዳማዊ ምኒልክ ዘር ውጪ የሚመጣን ተወዳዳሪ ቅስም ከመስበሩም በላይ በሰፊው የክርስትና ተከታይ ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ስለሚያገኝ እንደሆነ ይነገራል። በቀደሙ ጊዜያትም በዚህ ተቀፅላ ራሱን የገለፀው አፄ ኢያሱ አድያም ሰገድ ብቻ እንደነበር ታሪክ ያስረዳል ።
ያለፉት የኢትዮጵያ ነገስታት ማዕረግ ለምን "ዘእምነገደ ይሁዳ..." የሚለውን ተቀጽላ ያዘ?
ከኢትዮያዊው ንጉስ ተዋስያንና ከእናቷ ከእቴጌ ኤስሜኒ የተወለደችው ንግስተ ሳባ ተብላ የምትታወቀው የኢትዮጵያ ንግስት ከክርስቶስ ልደት በፊት1013 ዓመት (በ3,987 ዓመተ ዓለም) ላይ የነገሰች ናት። ስሟም ገንኖ የሚታወቅበት ምክንያት ንጉስ ሰለሞን የእስራኤል ንጉስ በነበረበት ዘመን ዝናውን ሰምታ ታምሪን በሚባለው ኢትዮጵያዊ ነጋዴ አማካኝነት ልትጎበኘው በመሄዷና ከተመለሰችም በሇላ ከንጉስ ሰለሞን እብነ እልኪም የተባለውን ልጇን ስለወለደለችለት ነው።
ንግስተ ሳባ ለ31 አመት ኢትዮጵያን ስታስተዳድር ከቆየች በሇላ መንግስቷን ከክርስቶስ ልደት በፊት በ982 አመት ለዚሁ ከንጉስ ሰለሞን ለተወለደው ልጇ ለእብነ እልኪም አውርሳ ቀዳማዊ ምኒልክ ወይም ዳዊት ተብሎ ነገሰ። ነግስተ ሳባ ከመልቀቇ በፊት የንግስና ስርዓት አውጥታለች። ስርአቱም "የኢትዮጵያን ዘውድ ጭኖ በትረ መንግስት ጨብጦ መግዛት ያለበት ከቀዳማዊ ምኒልክ ዘር የተወለደ እንዲሆን፣ መንግስትም ከእሱ ዘር እንዳይዎጣ" ብላ ከማስወሰኗም በላይ ከንግስተ ሳባ (ንግስት ማክዳ ወይም አዜብ) በሇላ "ከወንዱ ወገን እንጂ ከሴት ወገን የቀዳማዊ ምኒልክን ሥርወ መንግስት ዘውድ እንዳይጨብጥ" ስትል በህግ እንዲከለክል አደረገች።
ይህን ህግ የተከተለው የአነጋገስ ስርዐት ግን እየደከመ ሄዶ በ842 ዓ.ም ዮዲት የምትባል ንግስት ነግሳ ጭራሹኑ አጠፋችው። ቀጣዩ አልጋ ወራሽም ወደ ሸዋ ሸሸ። የቀሩት የቀዳማዊ ምኒልክ ተወላጆች ንጉሱን እንዳይቀናቀኑ በወቅቱ ደብረ ዳሞ መታገት ልማድ ስለነበረ እዚያው እንዳሉ በሙል ፈጀቻቸው።
ከዮዲት ዘመነ መንግስት በሇላ ግን በ882 ዓ.ም አንበሳ ውድም ከሸዋ ተመልሶ የአክሱምን መንግስት እንደገና ለሃያ አመት ዓጸና። ሆኖም ግን በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ትግሎች የንግስተ ሳባን ህግ በመጣስ ከምኒልክ ተወላጅ ያልሆኑ መሪዎች ስልጣኑን ሲይዙ ቆዩ። ቀረብ ባሉት ጊዜያትም አፄ ቴዎድሮስ እና ዓጼ ዮሐንስ ይህን ህግ ሳይከተሉ ስልጣኑን ከያዙት መሪዎች ውስጥ ይካተታሉ።
ዳግማዊ ምኒልክ ከአፄ ዮሐንሥ ህልፈተ ሕይወት በሇላ በ1882 ዓ.ም "ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ ዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ" ብለው በማዎጅ በቅርብ ከምኒልክ የዘር ሀረግ ወጥቶ የነበረውን የንግስና ማእረግ እንደገና መለሱ። ከአፄ ምኒልክ ቀጥሎ በዚሁ ተቀፅላ የነገሡት ንግሥተ ነገሥት ዘውዲቱ ፣ በሇላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ነበሩ። ከንጉሥ ሰሎሞንና ከንግስተ ሳባ ልጅ ከቀዳማዊ ምኒልክ አንስቶ ሲቆጠር ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ 225ኛ ንጉስ ናቸው።
ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ የሚለውን ተቀፅላ ንጉሶቹ ያወጁበት ማክንያት የይሁዳ ዘር የንጉስ ዳዊት ትውልድ ነን በማለት በሕዝብና በቀሳውስት ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኙ ስለሚፈልጉ እንደሆነ ይነገራል። በዚህም አይነት ሁኔታ ያለ ንጉስ ሲነግስ ከቀዳማዊ ምኒልክ ዘር ውጪ የሚመጣን ተወዳዳሪ ቅስም ከመስበሩም በላይ በሰፊው የክርስትና ተከታይ ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ስለሚያገኝ እንደሆነ ይነገራል። በቀደሙ ጊዜያትም በዚህ ተቀፅላ ራሱን የገለፀው አፄ ኢያሱ አድያም ሰገድ ብቻ እንደነበር ታሪክ ያስረዳል ።
