• PM Abiy Ahmed to Meet Ethiopian Community in Washington DC July 28th
    PM Abiy Ahmed to Meet Ethiopian Community in Washington DC July 28th
    0 Comments 0 Shares
  •  አሊ ቢራ፣ መሃሙድ አህመድ፣ ሃጫሉ ሁንዴሳ… በሚሊኒየም አዳራሽ ያዜማሉ    የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉላቸው ግብዣ መሰረት  ዛሬ ረፋድ ላይ ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገቡ ሲሆን ከቦሌ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ እስከ ቤተመንግስት ድረስ ደማቅ ህዝባዊ አቀባበል እንደሚደረግላቸው ታውቋል፡፡ከ20 ዓመታት በኋላ ወደ አዲስ አበባ የሚመጡት ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ፤ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፤ ከፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ እና ከአፍሪካ ህብረት ዋና ፀሃፊ ሙሣ ፋኪ ጋር ይወያያሉ ተብሏል፡፡ በሚሊኒየም አዳራሽ ነገ እሁድ ምሽት ለፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሚደረገው የእራት ግብዣ ላይ በርካታ ታዋቂ ድምጻውያን የኪነ ጥበብ ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አንጋፋው ድምፃዊ አሊ ቢራ፣ መሃመድ አህመድ፣ ጃኪ ጎሲ፣ ሃጫሉ ሁንዴሳ እና ሌሎችም ያቀነቅናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በኢትዮጵያ የ3 ቀናት ጉብኝት የሚያደርጉ ሲሆን የአዋሳውን የኢንዱትሪፓርክ ይጎበኟቸዋል ከተባሉት ውስጥ ይጠቀሳሉ፡፡ስታዲየም አካባቢ የሚገኘውና ቀድሞ የኤርትራ ኢምባሲ የነበረው ቢሮም በነገው እለት በይፋ “በኢትዮጵያ የኤርትራ ኢምባሲ” ሆኖ ስራውን ይጀምራል ተብሏል፡፡ባለፈው ሣምንት እሁድ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ በአስመራ እጅግ ደማቅና አስደማሚ አቀባበል የተደረገላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፤ በሁለቱ ሃገራት መካከል ይፋዊ እርቅ የሚፈጥር ባለ አምስት ነጥብ ስምምነት ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ተፈራርመው መመለሳቸው ይታወቃል፡፡ኤርትራ በ1983 ነፃነቷን ማግኘቷን ተከትሎ፣ ላለፉት 27 ዓመታት አገሪቷን በፕሬዚዳንትነት እየመሩ የሚገኙት የ72 አመቱ ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ፤ የሁለቱን ሃገራት ህዝቦች ለማቀራረብ ተከታታይ ስራዎችን እንደሚሠሩ ለሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ  አስታውቀዋል፡፡በአጭር ጊዜ ውስጥ በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል የፈነጠቀውን የሰላምና የተስፋ ብርሃን በተመለከተ የታሪክ ምሁሩ ፕ/ር ገብሩ ታረቀ ለአዲስ አድማስ በሰጡት አስተያየት፤ “በአግራሞትና በመደነቅ ነው ያየሁት፡፡ ምክንያቱም ሂደቱ በጣም ፈጣን ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አስመራ ሄደው ባለ አምስት ነጥብ ስምምነት መፈራረም ያልተጠበቀና አስገራሚ፣ አንዳንዴም አስደንጋጭ ሆኖ አገኘዋለሁ፡፡ ይህ የሠላም ስምምነት የቀጠናውን ሁኔታ ይቀይረዋል የሚል ግምት አለኝ፡፡” ብለዋል፡፡በኤርትራ አስመራ ልዩ ስሙ አባሻውል በተባለ ስፍራ የተወለዱት ኢሣያስ አፈወርቂ፤ የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአስመራ በሚገኘው ልኡል መኮንን ት/ቤት  ከተማሩ በኋላ ለከፍተኛ ትምህርት ወደ አዲስ አበባ መጥተው፣ የቀድሞው የቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዩኒቨርሲቲን የተቀላቀሉ ሲሆን የኢንጂነሪንግ ተማሪ እንደነበሩም ይታወቃል፡፡ እ.ኤ.አ በ1966 የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን በማቋረጥ በሱዳን በኩል ይንቀሳቀስ የነበረውን ኤርትራ ነፃነት ግንባርን እንደተቀላቀሉ ግለ ታሪካቸው ያመለክታል፡፡ በወጣትነታቸው በቻይና ከፍተኛ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠና ለሁለት አመታት የወሰዱት ኢሳያስ አፈወርቂ፤ 30 አመት የፈጀውን የኤርትራ የነፃነት ትግልን ከጓዶቻቸው ጋር እንደመሩ ይነገራል፡፡ ላለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ገደማም ኤርትራን በፕሬዚዳንትነት በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
     አሊ ቢራ፣ መሃሙድ አህመድ፣ ሃጫሉ ሁንዴሳ… በሚሊኒየም አዳራሽ ያዜማሉ    የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉላቸው ግብዣ መሰረት  ዛሬ ረፋድ ላይ ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገቡ ሲሆን ከቦሌ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ እስከ ቤተመንግስት ድረስ ደማቅ ህዝባዊ አቀባበል እንደሚደረግላቸው ታውቋል፡፡ከ20 ዓመታት በኋላ ወደ አዲስ አበባ የሚመጡት ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ፤ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፤ ከፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ እና ከአፍሪካ ህብረት ዋና ፀሃፊ ሙሣ ፋኪ ጋር ይወያያሉ ተብሏል፡፡ በሚሊኒየም አዳራሽ ነገ እሁድ ምሽት ለፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሚደረገው የእራት ግብዣ ላይ በርካታ ታዋቂ ድምጻውያን የኪነ ጥበብ ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አንጋፋው ድምፃዊ አሊ ቢራ፣ መሃመድ አህመድ፣ ጃኪ ጎሲ፣ ሃጫሉ ሁንዴሳ እና ሌሎችም ያቀነቅናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በኢትዮጵያ የ3 ቀናት ጉብኝት የሚያደርጉ ሲሆን የአዋሳውን የኢንዱትሪፓርክ ይጎበኟቸዋል ከተባሉት ውስጥ ይጠቀሳሉ፡፡ስታዲየም አካባቢ የሚገኘውና ቀድሞ የኤርትራ ኢምባሲ የነበረው ቢሮም በነገው እለት በይፋ “በኢትዮጵያ የኤርትራ ኢምባሲ” ሆኖ ስራውን ይጀምራል ተብሏል፡፡ባለፈው ሣምንት እሁድ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ በአስመራ እጅግ ደማቅና አስደማሚ አቀባበል የተደረገላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፤ በሁለቱ ሃገራት መካከል ይፋዊ እርቅ የሚፈጥር ባለ አምስት ነጥብ ስምምነት ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ተፈራርመው መመለሳቸው ይታወቃል፡፡ኤርትራ በ1983 ነፃነቷን ማግኘቷን ተከትሎ፣ ላለፉት 27 ዓመታት አገሪቷን በፕሬዚዳንትነት እየመሩ የሚገኙት የ72 አመቱ ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ፤ የሁለቱን ሃገራት ህዝቦች ለማቀራረብ ተከታታይ ስራዎችን እንደሚሠሩ ለሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ  አስታውቀዋል፡፡በአጭር ጊዜ ውስጥ በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል የፈነጠቀውን የሰላምና የተስፋ ብርሃን በተመለከተ የታሪክ ምሁሩ ፕ/ር ገብሩ ታረቀ ለአዲስ አድማስ በሰጡት አስተያየት፤ “በአግራሞትና በመደነቅ ነው ያየሁት፡፡ ምክንያቱም ሂደቱ በጣም ፈጣን ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አስመራ ሄደው ባለ አምስት ነጥብ ስምምነት መፈራረም ያልተጠበቀና አስገራሚ፣ አንዳንዴም አስደንጋጭ ሆኖ አገኘዋለሁ፡፡ ይህ የሠላም ስምምነት የቀጠናውን ሁኔታ ይቀይረዋል የሚል ግምት አለኝ፡፡” ብለዋል፡፡በኤርትራ አስመራ ልዩ ስሙ አባሻውል በተባለ ስፍራ የተወለዱት ኢሣያስ አፈወርቂ፤ የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአስመራ በሚገኘው ልኡል መኮንን ት/ቤት  ከተማሩ በኋላ ለከፍተኛ ትምህርት ወደ አዲስ አበባ መጥተው፣ የቀድሞው የቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዩኒቨርሲቲን የተቀላቀሉ ሲሆን የኢንጂነሪንግ ተማሪ እንደነበሩም ይታወቃል፡፡ እ.ኤ.አ በ1966 የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን በማቋረጥ በሱዳን በኩል ይንቀሳቀስ የነበረውን ኤርትራ ነፃነት ግንባርን እንደተቀላቀሉ ግለ ታሪካቸው ያመለክታል፡፡ በወጣትነታቸው በቻይና ከፍተኛ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠና ለሁለት አመታት የወሰዱት ኢሳያስ አፈወርቂ፤ 30 አመት የፈጀውን የኤርትራ የነፃነት ትግልን ከጓዶቻቸው ጋር እንደመሩ ይነገራል፡፡ ላለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ገደማም ኤርትራን በፕሬዚዳንትነት በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ዛሬ አዲስ አበባ ይገባሉ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> አሊ ቢራ፣ መሃሙድ አህመድ፣ ሃጫሉ ሁንዴሳ… በሚሊኒየም አዳራሽ ያዜማሉ<br /><br /> የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ ጠ/ሚኒስትር...
    0 Comments 0 Shares
  •  የፊታችን ማክሰኞ ሐምሌ 10 ቀን 2010 ዓ.ም የመጀመሪያውን በረራ ወደ አስመራ የሚያደርገው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ከ20 ዓመታት በኋላ 250 ሰዎችን ይዞ ወደ ኤርትራ አስመራ እንደሚጓዝ ተገለፀ፡፡ማክሰኞ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ከቦሌ አየር ማረፊያ የሚነሣው ቦይንግ 787 ዘመናዊ አውሮፕላን አስመራ ለመድረስ የ70 ደቂቃዎች ጊዜ ብቻ ይወስዳል ተብሏል፡፡ የአንድ ተጓዥ የደርሶ መልስ ቲኬት ዋጋም 8 ሺህ 944 ብር ሲሆን ይህም ወደ ሌሎች የጎረቤት ሃገራት ከሚደረገው የጉዞ ዋጋ አንፃር ዝቅተኛው ነው ተብሏል፡፡ ወደ ካርቱም ለመጓዝ 12172 ብር፣ ወደ ናይሮቢ 9779 ብር እንዲሁም ወደ ጅቡቲ 9561 ብር የደርሶ መልስ ቲኬት ዋጋ ሲሆን የአስመራው ጉዞ ከሁሉም ዝቅተኛው ነው፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እ.ኤ.አ ከግንቦት 1990 ጀምሮ የተቋረጠውን የአስመራ በረራ እንደሚጀምር ይፋ መደረጉንተከትሎ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ተጓዦች ጥያቄ ማቅረባቸው ታውቋል፡፡ኢትዮጵያውያን አስመራ ሲደርሱ ወዲያው የኤርትራ ቪዛ እንደሚያገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡
     የፊታችን ማክሰኞ ሐምሌ 10 ቀን 2010 ዓ.ም የመጀመሪያውን በረራ ወደ አስመራ የሚያደርገው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ከ20 ዓመታት በኋላ 250 ሰዎችን ይዞ ወደ ኤርትራ አስመራ እንደሚጓዝ ተገለፀ፡፡ማክሰኞ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ከቦሌ አየር ማረፊያ የሚነሣው ቦይንግ 787 ዘመናዊ አውሮፕላን አስመራ ለመድረስ የ70 ደቂቃዎች ጊዜ ብቻ ይወስዳል ተብሏል፡፡ የአንድ ተጓዥ የደርሶ መልስ ቲኬት ዋጋም 8 ሺህ 944 ብር ሲሆን ይህም ወደ ሌሎች የጎረቤት ሃገራት ከሚደረገው የጉዞ ዋጋ አንፃር ዝቅተኛው ነው ተብሏል፡፡ ወደ ካርቱም ለመጓዝ 12172 ብር፣ ወደ ናይሮቢ 9779 ብር እንዲሁም ወደ ጅቡቲ 9561 ብር የደርሶ መልስ ቲኬት ዋጋ ሲሆን የአስመራው ጉዞ ከሁሉም ዝቅተኛው ነው፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እ.ኤ.አ ከግንቦት 1990 ጀምሮ የተቋረጠውን የአስመራ በረራ እንደሚጀምር ይፋ መደረጉንተከትሎ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ተጓዦች ጥያቄ ማቅረባቸው ታውቋል፡፡ኢትዮጵያውያን አስመራ ሲደርሱ ወዲያው የኤርትራ ቪዛ እንደሚያገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    አየር መንገድ ማክሰኞ ወደ አስመራ የመጀመሪያ በረራውን ያደርጋል - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> የፊታችን ማክሰኞ ሐምሌ 10 ቀን 2010 ዓ.ም የመጀመሪያውን በረራ ወደ አስመራ የሚያደርገው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ከ20 ዓመታት በኋላ 250 ሰዎችን ይዞ ወ...
    0 Comments 0 Shares
  •  የኢትዮ-ኤርትራን ግጭትና የሁለቱን አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መቋረጥ ተከትሎ በግንቦት ወር 1990ዓ.ም የተዘጋው የቀድሞው የኤርትራ ኤምባሲ ከ20 አመታት ያህል በኋላ ነገ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በተገኙበት በይፋ እንደሚከፈት ይጠበቃል፡፡ከአዲስአበባ ስቴዲየም ፊት ለፊት የሚገኘው የቀድሞው የኤርትራ ኤምባሲ አስፈላጊው እድሳት እንደተደረገለትና ሁለቱ አገራት ባለፈው ሳምንት ባደረጉት ስምምነት መሰረት በይፋ ተከፍቶ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሚንስትር አቶ አህመድ ሽዴ ትናንትበሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ እያደረጉት ያለውንና ዛሬ የተጀመረውን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አስመልክተው አቶ አህመድ በሰጡት በዚሁ መግለጫ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ባለፈው ሳምንት በኤርትራ ባደረጉት ጉብኝት ሁለቱ አገራት ከተስማሙባቸው ጉዳዮች መካከል፣ ኤምባሲዎቻቸውን መልሶ መክፈት፣ የአየርትራንስፖርት እና የስልክ ግንኙነቶችን እንደገናማስጀመር የሚሉት እንደሚገኙበትም አቶአህመድ ሽዴ አስታውሰዋል።
     የኢትዮ-ኤርትራን ግጭትና የሁለቱን አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መቋረጥ ተከትሎ በግንቦት ወር 1990ዓ.ም የተዘጋው የቀድሞው የኤርትራ ኤምባሲ ከ20 አመታት ያህል በኋላ ነገ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በተገኙበት በይፋ እንደሚከፈት ይጠበቃል፡፡ከአዲስአበባ ስቴዲየም ፊት ለፊት የሚገኘው የቀድሞው የኤርትራ ኤምባሲ አስፈላጊው እድሳት እንደተደረገለትና ሁለቱ አገራት ባለፈው ሳምንት ባደረጉት ስምምነት መሰረት በይፋ ተከፍቶ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሚንስትር አቶ አህመድ ሽዴ ትናንትበሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ እያደረጉት ያለውንና ዛሬ የተጀመረውን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አስመልክተው አቶ አህመድ በሰጡት በዚሁ መግለጫ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ባለፈው ሳምንት በኤርትራ ባደረጉት ጉብኝት ሁለቱ አገራት ከተስማሙባቸው ጉዳዮች መካከል፣ ኤምባሲዎቻቸውን መልሶ መክፈት፣ የአየርትራንስፖርት እና የስልክ ግንኙነቶችን እንደገናማስጀመር የሚሉት እንደሚገኙበትም አቶአህመድ ሽዴ አስታውሰዋል።
    ADDISADMASSNEWS.COM
    የኤርትራ ኤምባሲ ከ20 አመታት በኋላ ነገ ይከፈታል - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> የኢትዮ-ኤርትራን ግጭትና የሁለቱን አገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መቋረጥ ተከትሎ በግንቦት ወር 1990ዓ.ም የተዘጋው የቀድሞው የኤርትራ ኤምባሲ ከ20 አመታት ያ...
    0 Comments 0 Shares
  •  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ሙስናንና ዘረኝነትን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ማጥፋትን ዋነኛ አጀንዳው አድርጎ እንደሚንቀሳቀስ አስታወቀ፡፡ የሙስና እና ጠባብነት መስፋፋት እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ዕጦት ቤተ ክርስቲያኒቱን ለከፍተኛ ክስና ወቀሳ እያጋለጣት እንደኾነ የተወያየው ቅዱስ ሲኖዶሱ፤ ችግሩን ለመፍታት ያስችላል ያለውን መሪ ዕቅድና የተለያዩ ጥናቶች ተግባራዊነት ዋነኛ አጀንዳው እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ ሐምሌ 3 ቀን 2010 ዓ.ም ያካሔደውን አስቸኳይ ስብሰባ ሲያጠናቅቅ፣ ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እንደተናገሩት፤ መልካም አስተዳደርን በቤተ ክርስቲያኒቱ የበለጠ ለማስፈን በባለሞያዎች የተዘጋጀው መሪ ዕቅድና ከአሁን በፊት የተጠኑ የመዋቅር፣ የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ጥናቶች በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ፣ ዋነኛ የመነጋገሪያ አጀንዳ ኾነው እንዲቀርቡ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡ በዋና አጀንዳነት የሚቀርበው መሪ ዕቅዱ፣ ወቅቱንና ዘመኑን በዋጀ መልኩ የቤተ ክርስቲያኒቱን የመልካም አስተዳደርና ሙስና ችግሮች ለመፍታት ያስችላል፤ ተብሏል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶሱ በአስቸኳይ ስብሰባው፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ወቅታዊና ዐበይት ችግሮች አጥንቶ ከመፍትሔዎቻቸው ጋር እንዲያቀርቡ የሠየመው ስድስት አባላት ያሉት የሊቃነ ጳጳሳት ኮሚቴ ያዘጋጀውን ጥናታዊ ጽሑፍ መነሻ በማድረግ በስፋት ተነጋግሯል፡፡ ለምልአተ ጉባኤው በቀረበው ፅሁፍ፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደር በተለይ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ ከቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር ጋራ ተያይዞ መልካም አስተዳደር ማስፈን አዳጋች መሆኑን፤ በአድባራትና ገዳማት ያለው የመሬት ወረራና በኪራይ ስም የሚፈፀም ሙስና መበራከቱን እንዲሁም ዘረኝነትንና ጎሠኝነትን መከላከል እንዳልተቻለ ተመልክቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ ያለባትን አጠቃላይ አስተዳደራዊ ችግር በጊዜ ባለመፍታቷ፣ የሚሰጠውን እርምትና ማስተካከያም ለመቀበል በጎ ፈቃድ ባለማሳየቷ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት፣ በፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር፣ በሰብአዊ መብት ኮሚሽንና በሰራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በኩል በተደጋጋሚ ለክስና ወቀሳ መጋለጧም ተጠቁሟል፡፡ ለሰብአዊ መብት መከበር ግንባር ቀደም ሆና መቆም የሚገባት ቤተ ክርስቲያኒቱ፣ በሰብአዊ መብት ጥሰት በቁጥር አንድ ደረጃ መቀመጧም አሳሳቢ ነው፤ ብሏል - ሪፖርቱ፡፡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎችና የአድባራትና ገዳማት ሰራተኞች፣ ምንጩ የማይታወቅ ሃብት ባለቤት መሆናቸውን ያተተው ጽሑፉ፤ በግልና በተደራጀ የቡድን ዝርፊያም ሠራተኞቹ ይታማሉ፤ ይህም ቤተ ክርስቲያኒቱን ለነቀፋና ትችት ዳርጓታል - ብሏል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶሱ በጥናታዊ ጽሑፉ የተጠቆሙ ዐበይት ወቅታዊ ችግሮችን ከተነጋገረባቸው በኋላ፣ ሦስት የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡ እነዚህም፣ ችግሮቹ ገዝፈው የሚታዩበትን የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከትን እንደገና ማዋቀርና ማደራጀት፤ በነበረው የአስተዳደርና የአሠራር ብልሽት ያለአግባብ ከሥራቸው የተፈናቀሉ ሠራተኞች ከሃይማኖት ሕጸጽና ከሙስና ነጻ መኾናቸው እየተገመገመ ወደ ሥራ እንዲመለሱ፤ በአጠቃላይ ከአዲስ አበባም ኾነ ክፍተት ካለባቸው አህጉረ ስብከት ሙስናንና ዘረኝነትን ለማጥፋት፣ ከዚህ በፊት በባለሞያዎች ተጠንቶ የተዘጋጀው መሪ ዕቅድ ተግባራዊ እንዲኾን በጥናታዊ ጽሑፉ የቀረበውን የመፍትሔ ሐሳብ ተቀብሎታል፡፡ በቀጣዩ የጥቅምት 2011 ምልዓተ ጉባኤም፣ ዋና የመነጋገሪያ አጀንዳ ኾኖ እንዲቀርብለት ወስኗል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶሱ በዚሁ አስቸኳይ ስብሰባው፣ ላለፉት 26 ዓመታት በአሜሪካ በስደት ከሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች ጋር የተፈጠረው አለመግባባት ተጀምሮ በቆየው ዕርቀ ሰላም እንዲያበቃ ሦስት ሊቃነ ጳጳሳትን በልዑክነት መሠየሙን አስታውቋል፡፡ ከመጪው ሐምሌ 11 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ፣ በዋሽንግተን ዲሲ የሚከናወነው የዕርቀ ሰላም ሂደት፣ 4ኛውን ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስን ጨምሮ በውጭ አገር የሚገኙ አባቶች ወደ አገር ውስጥ የሚገቡበትና ፍጹም የቤተ ክርስቲያን አንድነት የሚመለስበት ይኾናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ሐምሌ 21 እና 22 ቀን በዋሽንግተን ዲሲ እና በሎሳንጀለስ ከተሞች ከኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር የሚወያዩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለዕርቀ ሰላሙ ድጋፍ እንደሚሰጡም ታውቋል፡፡    
     የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ሙስናንና ዘረኝነትን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ማጥፋትን ዋነኛ አጀንዳው አድርጎ እንደሚንቀሳቀስ አስታወቀ፡፡ የሙስና እና ጠባብነት መስፋፋት እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ዕጦት ቤተ ክርስቲያኒቱን ለከፍተኛ ክስና ወቀሳ እያጋለጣት እንደኾነ የተወያየው ቅዱስ ሲኖዶሱ፤ ችግሩን ለመፍታት ያስችላል ያለውን መሪ ዕቅድና የተለያዩ ጥናቶች ተግባራዊነት ዋነኛ አጀንዳው እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ ሐምሌ 3 ቀን 2010 ዓ.ም ያካሔደውን አስቸኳይ ስብሰባ ሲያጠናቅቅ፣ ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እንደተናገሩት፤ መልካም አስተዳደርን በቤተ ክርስቲያኒቱ የበለጠ ለማስፈን በባለሞያዎች የተዘጋጀው መሪ ዕቅድና ከአሁን በፊት የተጠኑ የመዋቅር፣ የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ጥናቶች በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ፣ ዋነኛ የመነጋገሪያ አጀንዳ ኾነው እንዲቀርቡ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡ በዋና አጀንዳነት የሚቀርበው መሪ ዕቅዱ፣ ወቅቱንና ዘመኑን በዋጀ መልኩ የቤተ ክርስቲያኒቱን የመልካም አስተዳደርና ሙስና ችግሮች ለመፍታት ያስችላል፤ ተብሏል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶሱ በአስቸኳይ ስብሰባው፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ወቅታዊና ዐበይት ችግሮች አጥንቶ ከመፍትሔዎቻቸው ጋር እንዲያቀርቡ የሠየመው ስድስት አባላት ያሉት የሊቃነ ጳጳሳት ኮሚቴ ያዘጋጀውን ጥናታዊ ጽሑፍ መነሻ በማድረግ በስፋት ተነጋግሯል፡፡ ለምልአተ ጉባኤው በቀረበው ፅሁፍ፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደር በተለይ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ ከቅጥር፣ ዕድገትና ዝውውር ጋራ ተያይዞ መልካም አስተዳደር ማስፈን አዳጋች መሆኑን፤ በአድባራትና ገዳማት ያለው የመሬት ወረራና በኪራይ ስም የሚፈፀም ሙስና መበራከቱን እንዲሁም ዘረኝነትንና ጎሠኝነትን መከላከል እንዳልተቻለ ተመልክቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ ያለባትን አጠቃላይ አስተዳደራዊ ችግር በጊዜ ባለመፍታቷ፣ የሚሰጠውን እርምትና ማስተካከያም ለመቀበል በጎ ፈቃድ ባለማሳየቷ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት፣ በፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር፣ በሰብአዊ መብት ኮሚሽንና በሰራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በኩል በተደጋጋሚ ለክስና ወቀሳ መጋለጧም ተጠቁሟል፡፡ ለሰብአዊ መብት መከበር ግንባር ቀደም ሆና መቆም የሚገባት ቤተ ክርስቲያኒቱ፣ በሰብአዊ መብት ጥሰት በቁጥር አንድ ደረጃ መቀመጧም አሳሳቢ ነው፤ ብሏል - ሪፖርቱ፡፡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎችና የአድባራትና ገዳማት ሰራተኞች፣ ምንጩ የማይታወቅ ሃብት ባለቤት መሆናቸውን ያተተው ጽሑፉ፤ በግልና በተደራጀ የቡድን ዝርፊያም ሠራተኞቹ ይታማሉ፤ ይህም ቤተ ክርስቲያኒቱን ለነቀፋና ትችት ዳርጓታል - ብሏል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶሱ በጥናታዊ ጽሑፉ የተጠቆሙ ዐበይት ወቅታዊ ችግሮችን ከተነጋገረባቸው በኋላ፣ ሦስት የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡ እነዚህም፣ ችግሮቹ ገዝፈው የሚታዩበትን የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከትን እንደገና ማዋቀርና ማደራጀት፤ በነበረው የአስተዳደርና የአሠራር ብልሽት ያለአግባብ ከሥራቸው የተፈናቀሉ ሠራተኞች ከሃይማኖት ሕጸጽና ከሙስና ነጻ መኾናቸው እየተገመገመ ወደ ሥራ እንዲመለሱ፤ በአጠቃላይ ከአዲስ አበባም ኾነ ክፍተት ካለባቸው አህጉረ ስብከት ሙስናንና ዘረኝነትን ለማጥፋት፣ ከዚህ በፊት በባለሞያዎች ተጠንቶ የተዘጋጀው መሪ ዕቅድ ተግባራዊ እንዲኾን በጥናታዊ ጽሑፉ የቀረበውን የመፍትሔ ሐሳብ ተቀብሎታል፡፡ በቀጣዩ የጥቅምት 2011 ምልዓተ ጉባኤም፣ ዋና የመነጋገሪያ አጀንዳ ኾኖ እንዲቀርብለት ወስኗል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶሱ በዚሁ አስቸኳይ ስብሰባው፣ ላለፉት 26 ዓመታት በአሜሪካ በስደት ከሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች ጋር የተፈጠረው አለመግባባት ተጀምሮ በቆየው ዕርቀ ሰላም እንዲያበቃ ሦስት ሊቃነ ጳጳሳትን በልዑክነት መሠየሙን አስታውቋል፡፡ ከመጪው ሐምሌ 11 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ፣ በዋሽንግተን ዲሲ የሚከናወነው የዕርቀ ሰላም ሂደት፣ 4ኛውን ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስን ጨምሮ በውጭ አገር የሚገኙ አባቶች ወደ አገር ውስጥ የሚገቡበትና ፍጹም የቤተ ክርስቲያን አንድነት የሚመለስበት ይኾናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ሐምሌ 21 እና 22 ቀን በዋሽንግተን ዲሲ እና በሎሳንጀለስ ከተሞች ከኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር የሚወያዩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለዕርቀ ሰላሙ ድጋፍ እንደሚሰጡም ታውቋል፡፡    
    ADDISADMASSNEWS.COM
    ቤተ ክርስቲያኒቱ፡ ሙስናንና ዘረኝነትን ማጥፋት ዋነኛ አጀንዳዬ ይኾናል አለች የቀድሞው ፓትርያርክና የተሰደዱ ጳጳሳት ወደ አገር ይመለሳሉ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ሙስናንና ዘረኝነትን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ማጥፋትን ዋነኛ አጀንዳው አድርጎ እንደሚንቀሳቀስ አስታወቀ፡...
    0 Comments 0 Shares
  •  “ኢትዮጵያን መጠጊያ ላደረጉ ስደተኞችና ተቃዋሚዎች አስጊ ሁኔታ ተፈጥሯል”     በትጥቅ ትግል ታግዞ የሚንቀሳቀሰው የኤርትራ መንግስት ዋነኛው የፖለቲካ ተቃዋሚ ድርጅት፤ ኢትዮጵያና ኤርትራ እርቅ መፈፀማቸውን ተከትሎ፣ የአገሪቱ ስደተኞችና ተቃዋሚዎች የደህንነት ስጋት ውስጥ መውደቃቸውን አስታወቀ፡፡ የኤርትራ ብሄራዊ መድህን ግንባር የተሠኘውና ፅ/ቤቱን በአዲስ አበባ ያደረገው የኤርትራ መንግስት ዋነኛ ተቃዋሚ ድርጅት ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ፤ ከሠሞኑ በሁለቱ አገራት መካከል የተደረሰው እርቅ፣ ለህዝቦች ግንኙነት ጠቃሚ ቢሆንም በኤርትራ ያለውን “አምባገነን” ስርአት ሸሽተው፣ ኢትዮጵያን መጠጊያ ላደረጉ በመቶ ሺዎች ለሚቆጠሩ ስደተኞችና ተቃዋሚዎች አስጊ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቁሟል፡፡ ኢትዮጵያ የድንበር ኮሚሽኑን ውሣኔ ተግባራዊ ለማድረግ በመወሰኗ ደስተኛ ነን ያለው  ግንባሩ፤ ይሁን እንጂ በኤርትራ ዲሞክራሲያዊ ስርአት እውን ሳይሆን በቀጠናው ሠላምና መረጋጋት ሊመጣ አይችልም ብሏል፡፡የኢትዮጵያ መንግስት፤ በኤርትራ ያለውን የዲሞክራሲ እጦት አጢኖ፣ ከፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ ጋር እየመሠረተ ያለውን ወዳጅነት በጥንቃቄ እንዲመረምር ግንባሩ በመግለጫው ጠይቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የወሰዱትን ተራማጅ እርምጃ እናደንቃለን ያለው ግንባሩ፤ እርምጃው በሁለቱ ህዝቦች መካከል መቀራረብን እንደሚፈጥርና የህዝቡ መቀራረብ ደግሞ ለሚፈለገው ዲሞክራሲያዊ ለውጥ አስፈላጊ መሆኑን አልሸሸገም፡፡እንዲያም ሆኖ የተፈጠረው ግንኙነት በኢትዮጵያ ላሉ አባሎቼ አስጊ ሆኗል ያለው የኤርትራ ብሄራዊ መድህን ግንባር፤ የኢትዮጵያ መንግስትና የአካባቢው ሃገራት በኤርትራ ዲሞክራሲያዊ ስርአት እንዲገነባና የዜጎች ነፃነትና ፍትህ እንዲረጋገጥ እገዛ እንዲያደርጉ ጠይቋል፡፡ግንባሩ ይሄን ስጋቱን በተመለከተም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት በደብዳቤ ማሳወቁን ጠቁሟል፡፡  “እኛ ሠላም አንጠላም፤ በኤርትራ ያለው ሁኔታ እንዲለወጥ እንፈልጋለን፤ የኢትዮጵያ መንግስትም ይህን ያገናዘበ በሣል እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን” ብሏል - ግንባሩ፡፡
     “ኢትዮጵያን መጠጊያ ላደረጉ ስደተኞችና ተቃዋሚዎች አስጊ ሁኔታ ተፈጥሯል”     በትጥቅ ትግል ታግዞ የሚንቀሳቀሰው የኤርትራ መንግስት ዋነኛው የፖለቲካ ተቃዋሚ ድርጅት፤ ኢትዮጵያና ኤርትራ እርቅ መፈፀማቸውን ተከትሎ፣ የአገሪቱ ስደተኞችና ተቃዋሚዎች የደህንነት ስጋት ውስጥ መውደቃቸውን አስታወቀ፡፡ የኤርትራ ብሄራዊ መድህን ግንባር የተሠኘውና ፅ/ቤቱን በአዲስ አበባ ያደረገው የኤርትራ መንግስት ዋነኛ ተቃዋሚ ድርጅት ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ፤ ከሠሞኑ በሁለቱ አገራት መካከል የተደረሰው እርቅ፣ ለህዝቦች ግንኙነት ጠቃሚ ቢሆንም በኤርትራ ያለውን “አምባገነን” ስርአት ሸሽተው፣ ኢትዮጵያን መጠጊያ ላደረጉ በመቶ ሺዎች ለሚቆጠሩ ስደተኞችና ተቃዋሚዎች አስጊ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቁሟል፡፡ ኢትዮጵያ የድንበር ኮሚሽኑን ውሣኔ ተግባራዊ ለማድረግ በመወሰኗ ደስተኛ ነን ያለው  ግንባሩ፤ ይሁን እንጂ በኤርትራ ዲሞክራሲያዊ ስርአት እውን ሳይሆን በቀጠናው ሠላምና መረጋጋት ሊመጣ አይችልም ብሏል፡፡የኢትዮጵያ መንግስት፤ በኤርትራ ያለውን የዲሞክራሲ እጦት አጢኖ፣ ከፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ ጋር እየመሠረተ ያለውን ወዳጅነት በጥንቃቄ እንዲመረምር ግንባሩ በመግለጫው ጠይቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የወሰዱትን ተራማጅ እርምጃ እናደንቃለን ያለው ግንባሩ፤ እርምጃው በሁለቱ ህዝቦች መካከል መቀራረብን እንደሚፈጥርና የህዝቡ መቀራረብ ደግሞ ለሚፈለገው ዲሞክራሲያዊ ለውጥ አስፈላጊ መሆኑን አልሸሸገም፡፡እንዲያም ሆኖ የተፈጠረው ግንኙነት በኢትዮጵያ ላሉ አባሎቼ አስጊ ሆኗል ያለው የኤርትራ ብሄራዊ መድህን ግንባር፤ የኢትዮጵያ መንግስትና የአካባቢው ሃገራት በኤርትራ ዲሞክራሲያዊ ስርአት እንዲገነባና የዜጎች ነፃነትና ፍትህ እንዲረጋገጥ እገዛ እንዲያደርጉ ጠይቋል፡፡ግንባሩ ይሄን ስጋቱን በተመለከተም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት በደብዳቤ ማሳወቁን ጠቁሟል፡፡  “እኛ ሠላም አንጠላም፤ በኤርትራ ያለው ሁኔታ እንዲለወጥ እንፈልጋለን፤ የኢትዮጵያ መንግስትም ይህን ያገናዘበ በሣል እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን” ብሏል - ግንባሩ፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    የኤርትራ ተቃዋሚ ግንባር ስጋት ውስጥ መውደቁን ገለጸ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> “ኢትዮጵያን መጠጊያ ላደረጉ ስደተኞችና ተቃዋሚዎች አስጊ ሁኔታ ተፈጥሯል”<br /><br /><br /> በትጥቅ ትግል ታግዞ የሚንቀሳ...
    0 Comments 0 Shares
  • በዓመት አንድ ቢሊየን ብር ገደማ የኮንትሮባንድ ዕቃ ይገባል    የኢትዮጵያ መንግስት ኢ መደበኛ የጠረፍ ንግድን የሚያበረታታ የህግ ማዕቀፍና ልዝብ የድንበር ፖሊሲ (Soft boarder policy)  ቀርጾ ሊተገብር እንደሚገባ፣ አንድ የአዲስ አበባ ምሁር ሲገልጹ፤  በዓመት በአማካይ አንድ ቢሊየን ብር የሚገመት ኮንትሮባንድ ዕቃ ከውጭ ወደ ሐገር ውስጥ እንደሚገባ የፌዴራል ገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣን ባልደረባ አመለከቱ፡፡‹‹ድንበር የማዕከሉ መስታወት ወይም ነጸብራቅ ነው፡፡ የድንበር ጉዳይ ከጸጥታ ሥራ ጋር ብቻ ተቆራኝቶ መታየት አይኖርበትም›› ያሉት ‹‹የምሥራቅ አፍሪካ የጠረፍ ከተሞች እንቅስቃሴ›› (Borederland Dynamics in East Africa) በሚል ርዕስ የሚካሄድ የጥናት ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶ/ር ፍቃዱ አዱኛ፤ የአፍሪካ የድንበር አካባቢዎች የሚታዩት ታሪካዊና ማህበረሰባዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች መንግስታት ‹‹ለዘብ ያለ የድንበር ፖሊሲ›› (Soft boarder policy) እንዲቀርጹ የሚያስገድዱ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።መንግስታት ጥብቅ የሆነ ድንበር ፖሊሲ ሲከተሉ በጠረፍ አካባቢ የሚኖረው ማህበረሰብ እንደሚጎዳ የገለጹትና ህይወቱን ሊያሻሻሽሉ የሚችሉ አካባቢያዊ ምቹ ሁኔታዎችን ወይም በእጁ ያለውን ሐብት መጠቀም እንዳይችል ያደርገዋል ያሉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲው መምህር ዶ/ር ፍቃዱ፤ ጥብቅ የጉምሩክ ህጎች ከጠረፍ ንግድ ሥራ በቀር ሌላ የኑሮ መሠረት የሌላቸውን ዜጎች ህይወት ፈታኝ ያደርገዋል ብለዋል፡፡መንግስት ለድንበር ጉዳዮች በቂ ትኩረት አልሰጠም በሚል ወቀሳ የሰነዘሩ የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች፤ ከቅኝ ግዛት ጋር ተያይዞ የተፈጠሩና ለመቶ ዓመታት መፍትሔ ሳያገኙ እየተንከባለሉ የመጡ የድንበር ችግሮች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ ችግሩን አቅልለን በማየት ትኩረት ሳንሰጠው የምንቀጥል ከሆነ፣ በጣት በሚቆጠሩ በዓመታት በርካታ ውጥንቅጥ ውስጥ እንደሚከተን መሪዎቻችን እንዲገነዘቡ ማድረግ ይኖርባቸኋል በማለት ለምሁራኑ አደራ ሰጥተዋል፡፡አውደ ጥናቱ በዓለም አቀፍ ድንበር ላይ ያተኮረ ቢሆንም በውይይቱ በክልሎች መካከል ያሉ የአስተዳደር ወሰን ችግሮችም ይነሱ ነበር፡፡ ‹‹የአስተዳደር ወሰኖችን ድንበር አድርጎ የማየት ዝንባሌ ተበራክቷል፡፡ ግጭት በዝቷል፡፡  እንደ ቀድሞው በድንበርና በአስተዳደር ወሰኖች አካባቢ በሚኖሩ የተለያዩ ብሔረሰቦች መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን በሽማግሌዎች አማካይነት መፍታት የማይቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል›› የሚሉ አስተያየት ሰጪዎችም ተደምጠዋል፡፡ በመንግስት ውሳኔ ያገኙ የአስተዳደር ወሰን ችግሮች ጭምር ተፈጻሚ  ሳይሆኑ ከአስር ዓመታት በላይ መቆየታቸውን በአብነት በመጥቀስ ወቀሳ ያቀረቡ የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች፤ በድንበር አካባቢ የሚታዩ አንዳንድ ችግሮች ከመልካም አስተዳደር እጦት ጋር እንደሚያያዙ ጠቅሰው፤ ‹‹መሬታችን ተነጥቆ ለኢንቨስተር ተሰጠብን፤ ካሣ በአግባቡ አላገኘንም›› በሚል ቅሬታ የሚሸፍቱ ሰዎች መኖራቸውን አመልክተዋል፡፡ በሌላ በኩል፤ የቁም ከብት ንግድ ፈቃድ በተወሰኑ ሰዎች መያዙንና እነዚህ ንግድ ፈቃድ ያላቸው ሰዎች ከብት ሳያረቡ ወይም ሳያደልቡ የቁም ከብት ወደ ውጭ በመውሰድ ለመሸጥ ከሚፈልጉ ፈቃድ የሌላቸው ነጋዴዎች በከብት ሰባት መቶ ብር እያስከፈሉ ያለ ሥራ ገንዘብ የሚሰበስቡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የፌዴራል ገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣንን በመወከል በአውደ ጥናቱ የተሳተፉ አንድ ግለሰብ እንደ ገለጹት፤ ከሚደረገው ቁጥጥር ብልሹነት ወይም ደካማነት የተነሳ የሚያልፈው የኮንትሮባንድ ዕቃ ከሚያዘው በብዙ እጥፍ እንደሚበልጥ ጠቅሰው፤ ‹‹በዓመት ከ400 -500 ሚሊየን ብር የኮንትሮባንድ ዕቃ ይያዛል፡፡ ይህም አኃዝ በ2008 ዓ.ም 905 ሚሊየን ብር ደርሶ ነበር። ሆኖም በ2009 እና 2010 ዓ.ም በዓመት ወደ አንድ ቢሊየን ብር ገደማ የሚገመት የኮንትሮባንድ ዕቃ ወደ መሐል ሀገር ገብቷል፡፡ ወደ ሐገር ቤት ከሚገባው የኮንትሮባንድ ዕቃም ውስጥ በብዙ ሚሊየን ብር የሚገመት የጦር መሣሪያ፣ አደንዛዥ ዕጽ እና መድኃኒት ነው›› ብለዋል፡፡በኮንትሮባንድ ንግድ የተሰማሩት ወገኖች፣ በጣም የረቀቀ ስልት እንደሚጠቀሙና በአሁኑ ሰዓት ከተቆጣጣሪው ይልቅ ኮንትሮባንዲስቱ የረቀቀ የቴክኖሎጂ አቅም እንዳለው ጠቅሰው፤ ነፍስ ባለው ዶሮ ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃ በመደበቅ በኮንትሮባንድ ለማስገባት ጥረት እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡  (ዝርዝሩን በገጽ ……)
    በዓመት አንድ ቢሊየን ብር ገደማ የኮንትሮባንድ ዕቃ ይገባል    የኢትዮጵያ መንግስት ኢ መደበኛ የጠረፍ ንግድን የሚያበረታታ የህግ ማዕቀፍና ልዝብ የድንበር ፖሊሲ (Soft boarder policy)  ቀርጾ ሊተገብር እንደሚገባ፣ አንድ የአዲስ አበባ ምሁር ሲገልጹ፤  በዓመት በአማካይ አንድ ቢሊየን ብር የሚገመት ኮንትሮባንድ ዕቃ ከውጭ ወደ ሐገር ውስጥ እንደሚገባ የፌዴራል ገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣን ባልደረባ አመለከቱ፡፡‹‹ድንበር የማዕከሉ መስታወት ወይም ነጸብራቅ ነው፡፡ የድንበር ጉዳይ ከጸጥታ ሥራ ጋር ብቻ ተቆራኝቶ መታየት አይኖርበትም›› ያሉት ‹‹የምሥራቅ አፍሪካ የጠረፍ ከተሞች እንቅስቃሴ›› (Borederland Dynamics in East Africa) በሚል ርዕስ የሚካሄድ የጥናት ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶ/ር ፍቃዱ አዱኛ፤ የአፍሪካ የድንበር አካባቢዎች የሚታዩት ታሪካዊና ማህበረሰባዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች መንግስታት ‹‹ለዘብ ያለ የድንበር ፖሊሲ›› (Soft boarder policy) እንዲቀርጹ የሚያስገድዱ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።መንግስታት ጥብቅ የሆነ ድንበር ፖሊሲ ሲከተሉ በጠረፍ አካባቢ የሚኖረው ማህበረሰብ እንደሚጎዳ የገለጹትና ህይወቱን ሊያሻሻሽሉ የሚችሉ አካባቢያዊ ምቹ ሁኔታዎችን ወይም በእጁ ያለውን ሐብት መጠቀም እንዳይችል ያደርገዋል ያሉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲው መምህር ዶ/ር ፍቃዱ፤ ጥብቅ የጉምሩክ ህጎች ከጠረፍ ንግድ ሥራ በቀር ሌላ የኑሮ መሠረት የሌላቸውን ዜጎች ህይወት ፈታኝ ያደርገዋል ብለዋል፡፡መንግስት ለድንበር ጉዳዮች በቂ ትኩረት አልሰጠም በሚል ወቀሳ የሰነዘሩ የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች፤ ከቅኝ ግዛት ጋር ተያይዞ የተፈጠሩና ለመቶ ዓመታት መፍትሔ ሳያገኙ እየተንከባለሉ የመጡ የድንበር ችግሮች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ ችግሩን አቅልለን በማየት ትኩረት ሳንሰጠው የምንቀጥል ከሆነ፣ በጣት በሚቆጠሩ በዓመታት በርካታ ውጥንቅጥ ውስጥ እንደሚከተን መሪዎቻችን እንዲገነዘቡ ማድረግ ይኖርባቸኋል በማለት ለምሁራኑ አደራ ሰጥተዋል፡፡አውደ ጥናቱ በዓለም አቀፍ ድንበር ላይ ያተኮረ ቢሆንም በውይይቱ በክልሎች መካከል ያሉ የአስተዳደር ወሰን ችግሮችም ይነሱ ነበር፡፡ ‹‹የአስተዳደር ወሰኖችን ድንበር አድርጎ የማየት ዝንባሌ ተበራክቷል፡፡ ግጭት በዝቷል፡፡  እንደ ቀድሞው በድንበርና በአስተዳደር ወሰኖች አካባቢ በሚኖሩ የተለያዩ ብሔረሰቦች መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን በሽማግሌዎች አማካይነት መፍታት የማይቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል›› የሚሉ አስተያየት ሰጪዎችም ተደምጠዋል፡፡ በመንግስት ውሳኔ ያገኙ የአስተዳደር ወሰን ችግሮች ጭምር ተፈጻሚ  ሳይሆኑ ከአስር ዓመታት በላይ መቆየታቸውን በአብነት በመጥቀስ ወቀሳ ያቀረቡ የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች፤ በድንበር አካባቢ የሚታዩ አንዳንድ ችግሮች ከመልካም አስተዳደር እጦት ጋር እንደሚያያዙ ጠቅሰው፤ ‹‹መሬታችን ተነጥቆ ለኢንቨስተር ተሰጠብን፤ ካሣ በአግባቡ አላገኘንም›› በሚል ቅሬታ የሚሸፍቱ ሰዎች መኖራቸውን አመልክተዋል፡፡ በሌላ በኩል፤ የቁም ከብት ንግድ ፈቃድ በተወሰኑ ሰዎች መያዙንና እነዚህ ንግድ ፈቃድ ያላቸው ሰዎች ከብት ሳያረቡ ወይም ሳያደልቡ የቁም ከብት ወደ ውጭ በመውሰድ ለመሸጥ ከሚፈልጉ ፈቃድ የሌላቸው ነጋዴዎች በከብት ሰባት መቶ ብር እያስከፈሉ ያለ ሥራ ገንዘብ የሚሰበስቡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የፌዴራል ገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣንን በመወከል በአውደ ጥናቱ የተሳተፉ አንድ ግለሰብ እንደ ገለጹት፤ ከሚደረገው ቁጥጥር ብልሹነት ወይም ደካማነት የተነሳ የሚያልፈው የኮንትሮባንድ ዕቃ ከሚያዘው በብዙ እጥፍ እንደሚበልጥ ጠቅሰው፤ ‹‹በዓመት ከ400 -500 ሚሊየን ብር የኮንትሮባንድ ዕቃ ይያዛል፡፡ ይህም አኃዝ በ2008 ዓ.ም 905 ሚሊየን ብር ደርሶ ነበር። ሆኖም በ2009 እና 2010 ዓ.ም በዓመት ወደ አንድ ቢሊየን ብር ገደማ የሚገመት የኮንትሮባንድ ዕቃ ወደ መሐል ሀገር ገብቷል፡፡ ወደ ሐገር ቤት ከሚገባው የኮንትሮባንድ ዕቃም ውስጥ በብዙ ሚሊየን ብር የሚገመት የጦር መሣሪያ፣ አደንዛዥ ዕጽ እና መድኃኒት ነው›› ብለዋል፡፡በኮንትሮባንድ ንግድ የተሰማሩት ወገኖች፣ በጣም የረቀቀ ስልት እንደሚጠቀሙና በአሁኑ ሰዓት ከተቆጣጣሪው ይልቅ ኮንትሮባንዲስቱ የረቀቀ የቴክኖሎጂ አቅም እንዳለው ጠቅሰው፤ ነፍስ ባለው ዶሮ ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃ በመደበቅ በኮንትሮባንድ ለማስገባት ጥረት እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡  (ዝርዝሩን በገጽ ……)
    ADDISADMASSNEWS.COM
    ‹‹መንግስት ለድንበር ጉዳዮች በቂ ትኩረት አልሰጠም›› - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;">በዓመት አንድ ቢሊየን ብር ገደማ የኮንትሮባንድ ዕቃ ይገባል<br /><br /> የኢትዮጵያ መንግስት ኢ መደበኛ የጠረፍ ንግድን የሚያበረታታ የህ...
    0 Comments 0 Shares
  •      የአማራ ክልል ርዕሠ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ዛሬ ከሃረሚያ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት እንደሚሠጣቸው የታወቀ ሲሆን ከሳምንት በፊት የኦሮሚያ ክልል ርዕሠ መስተዳደር አቶ ለማ መገርሣ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ተቀብለዋል፡፡ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የክብር ዶክትሬቱ የሚሠጣቸው በክልላቸው ላሣዩት የአመራር ጥበብ እውቅና ከመስጠት አንፃር መሆኑን ምንጮች ለአዲስ አድማስ የጠቆሙ ሲሆን ሃረማያ ዩኒቨርሲቲ ከተቋቋመ ጀምሮ የክብር ዶክትሬት የሠጣቸው ሶስተኛው ሰው ይሆናሉ ተብሏል፡፡ከአቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጋር የመጀመሪያው የኦሮሚኛ ቋንቋ ጋዜጠኛ የሆኑት እና የተለያዩ የኦሮሚኛ ስነ ጥበባዊ ስራዎችን ያበረከቱት አርቲስት መሃመድ አህመድ ቆጴም የክብር ዶክትሬት እንደሚሰጣቸው ታውቋል፡፡ሃረሚያ ዩኒቨርሲቲ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ የክብር ዶክትሬት የሠጠው ለሁለት ግለሠቦች ብቻ መሆኑ የታወቀ ሲሆን እነሡም የጅቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ እና ታዋቂው ሳይንቲስት ፕሮፌሠር ኢጄታ ገቢሣ ናቸው፡፡ ሃረሚያ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት 7 ሺህ 900 ተማሪዎችን በተለያዩ መርሃ ግብሮች እንደሚያስመርቅ ታውቋል፡፡በሌላ በኩል ሠኔ 30 ቀን 2010 ዓ.ም የጅማ ዩኒቨርሲቲ በኦሮሚያ ክልል ለሠጡት በሣል አመራር ለክልሉ ፕሬዚዳንት ለማ መገርሣ የክብር ዶክተሬት ሰጥቷቸዋል፡፡
         የአማራ ክልል ርዕሠ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ዛሬ ከሃረሚያ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት እንደሚሠጣቸው የታወቀ ሲሆን ከሳምንት በፊት የኦሮሚያ ክልል ርዕሠ መስተዳደር አቶ ለማ መገርሣ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ተቀብለዋል፡፡ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የክብር ዶክትሬቱ የሚሠጣቸው በክልላቸው ላሣዩት የአመራር ጥበብ እውቅና ከመስጠት አንፃር መሆኑን ምንጮች ለአዲስ አድማስ የጠቆሙ ሲሆን ሃረማያ ዩኒቨርሲቲ ከተቋቋመ ጀምሮ የክብር ዶክትሬት የሠጣቸው ሶስተኛው ሰው ይሆናሉ ተብሏል፡፡ከአቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጋር የመጀመሪያው የኦሮሚኛ ቋንቋ ጋዜጠኛ የሆኑት እና የተለያዩ የኦሮሚኛ ስነ ጥበባዊ ስራዎችን ያበረከቱት አርቲስት መሃመድ አህመድ ቆጴም የክብር ዶክትሬት እንደሚሰጣቸው ታውቋል፡፡ሃረሚያ ዩኒቨርሲቲ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ የክብር ዶክትሬት የሠጠው ለሁለት ግለሠቦች ብቻ መሆኑ የታወቀ ሲሆን እነሡም የጅቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ እና ታዋቂው ሳይንቲስት ፕሮፌሠር ኢጄታ ገቢሣ ናቸው፡፡ ሃረሚያ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት 7 ሺህ 900 ተማሪዎችን በተለያዩ መርሃ ግብሮች እንደሚያስመርቅ ታውቋል፡፡በሌላ በኩል ሠኔ 30 ቀን 2010 ዓ.ም የጅማ ዩኒቨርሲቲ በኦሮሚያ ክልል ለሠጡት በሣል አመራር ለክልሉ ፕሬዚዳንት ለማ መገርሣ የክብር ዶክተሬት ሰጥቷቸዋል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ዛሬ ከሃረሚያ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ይቀበላሉ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"><br /> የአማራ ክልል ርዕሠ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ዛሬ ከሃረሚያ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት እንደሚሠጣቸው የታወቀ ሲሆን ከሳምንት በፊት...
    0 Comments 0 Shares