• AMHARIC.VOANEWS.COM
    በአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የዕጩ ምክትል ፕሬዚዳንቶች የአሸናፊነት ሚና ምን ያህል ነው?
    በዩናይትድ ስቴትስ፣ በኅዳር ወር በሚካሔደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የሚወዳደሩት የዴሞክራቲክ ፓርቲው እና የሪፐብሊካን ፓርቲው ዕጩ ፕሬዚዳንቶች፣ አብረዋቸው የሚወዳደሩትን ዕጩ ምክትል ፕሬዚዳንቶችን መርጠዋል፡፡ አሁን ጥያቄው፣ አጣማሪ ዕጩዎቻቸው በምርጫው እንዲያሸንፉ ምን ያህል ይረዷቸው ይኾን? የሚለው ነው፡፡ የቪኦኤዋ ቬሮኒካ ኢግሊሲያስ ባልዴራስ፣ በአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫዎች ታሪክ፣ የዕጩ ምክትል ፕሬዚዳንቶችን ሚና በመዳሰስ፣ የአሁኖቹ ዕጩዎች ቲም ዎልዝ እና...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ሸምጋዮች የተኩስ አቁም ግፊት ሲያደርጉ የእስራኤል ወታደሮች በጋዛ አዲስ ጥቃት ሰነዘሩ
    ዩናይትድ ስቴትስ፣ ካታር እና ግብፅ እስራኤል እና ሃማስ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደርሱ እየገፋፏቸው ባለበት ወቅት የእስራኤል ወታደሮች ዛሬ አርብ በደቡባዊ ጋዛ ካን ዮኒስ ከተማ አዲስ ጥቃት ሰንዝረዋል። የእስራኤል ኃይሎች የሚያካሂዱት ተደጋጋሚ ጥቃት ቢሰነዘርባቸውም አሁንም በአካባቢው እንደሚንቀሳቀሱ የሚናገሩትን የሃማስ ተዋጊዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መሆኑን ተናገረዋል። የእስራኤል ወታደሮች ባለፈው ሀምሌ ጥቃት ከሰነዘሩበትና ከባድ ውድመት ከደረሰበት...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የካታሎኒያ መገንጠል መሪ ስፔይን ገብተው ወጡ
    የካታሎኒያ ተገንጣይ መሪ ካርሌስ ፑችዴሞን በባርሴሎና በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ላይ ከታዩ በኋላ ስፔይንን ለቀው ወደ ቤልጂየም ሄዱ። የፓርቲያቸው ዋና ጸሀፊ ዛሬ ዓርብ በሰጡት መግለጫ ፑችዴሞን ስፔይን ውስጥ እንዲያዙ የእስር ማዘዣ ወጥቶባቸዋል ብለዋል፡፡ ይሁን እንጂ ፑችደሞን ከሀገር በመሸሽ ራሳቸውን በግዞት በሚያኖሩባት ዋተርሉ ቤልጂየም ስለመድረሳቸው እንደማያውቁ ዋና ጸሀፊው ጆርዲ ቱሩል ተናግረዋል፡፡ እኤአ ካታሎኒያን ከስፔይን ለመገንጠል ያደረጉት ሙከራ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የፊፋና የአፍሪካ ስፖርት መሪው ኢሳ ሃያቱ አረፉ
    በአፍሪካ እግር ኳስ ታሪክ ትቅል ስፍራ የነበራቸው ቀድሞው የፊፋ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት እና የረጅም ጊዜ የአፍሪካ እግር ኳስ መሪ ኢሳ ሀያቱ በ77 ዓመታቸው ፓሪስ ውስጥ ትላንት ሀሙስ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። የወቅቱ የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በኢንስታግራም ገፃቸው ላይ “የቀድሞው የካፍ ፕሬዝዳንት፣ የፊፋ ጊዚያዊ ፕሬዝዳንት እና የፊፋ ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሁም የፊፋ ምክር ቤት አባል ኢሳ ሀያቱ በማለፋቸው አዝኛለሁ" ብለዋል፡፡ የ2024 ኦሎምፒክ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የኢትዮጵያና የሶማሊያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ሁለተኛ ዙር ውይይት ሊያደርጉ ነው
    ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋራ የፈረመችው የባሕር በር አጠቃቀም ስምምነት የፈጠረውን አለመግባባት በተመለከተ፣ የኢትዮጵያና የሶማሊያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር በሚቀጥለው ሳምንት አንካራ ላይ ተገናኝተው ለሁለተኛ ዙር እንደሚወያዩ የቱርክ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን ዛሬ ዓርብ አስታወቀዋል። ታኅሳስ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ፣ ወይም በያዝነው የፈረንጆች ዓመት በመጀመሪያው ቀን፣ ኢትዮጵያ 20 ኪ/ሜ የሚደርስ የባሕር ዳርቻ ከሶማሊላንድ በሊዝ ለመያዝ ስምምነት መፈራረሟ፣...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የህወሓት አመራሮች ጉዳይ
    በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ(ህወሓት) የፖለቲካ አመራር መካከል ያለው አለመግባባት፣ የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት መፈረም ከቆመ በኋላ እየሰፋ መምጣቱን፣ አመራሮቹ የሚሰጧቸው የተናጠል መግለጫዎች ያመለክታሉ፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ባለፈው ሰኞ፣ ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም. ለድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ በፓርቲው ውስጥ ልዩነቶች እየሰፉ መምጣታቸውን ጠቁመዋል፡፡ ይኸው...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ምርጫ ቦርድ ህወሓትን “በልዩ ኹኔታ” መዘገበው
    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ(ህ.ወ.ሓ.ት)፣ የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ “በልዩ ኹኔታ” መስጠቱን፣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ህወሓት፣ ዳግም ሕጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስለት፣ በተለያዩ ጊዜያት በተደጋጋሚ ያቀረበውን ጥያቄ ያስታወሰው ቦርዱ፣ በቀድሞው ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011ም ኾነ በተሻሻለው ዐዋጅ ቁጥር 1332/2016 መሠረት፣ በዐመፃ ተግባር ላይ ተሰማርቶ ሕጋዊ ሰውነቱ ለተሰረዘ ፓርቲ የቀድሞ ህልውናውን መልሶ የሚሰጥ...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የሸበሌ ወንዝ ሙላት በሁለት የሶማሌ ክልል ወረዳዎች ሰብሎችን ማውደሙ ተገለጸ
    በባሌ ተራራማ ስፍራዎች የጣለውን ከባድ ዝናም ተከትሎ ከወሰኑ አልፎ የሞላው የሸበሌ ወንዝ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በሶማሌ ክልል ሁለት ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ የእርሻ ማሳዎችን ማውደሙ ተገለጸ፡፡ ባለፉት ሦስት ዓመታት፣ ነዋሪዎችን ከወንዙ ዳርቻ በማንሣት በከፍተኛ ቦታዎች የማስፈር ሥራ መሠራቱን ያስታወሰው የክልሉ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ፣ ጎርፉ፥ በሰው፣ በእንስሳት እና በመሠረተ ልማት ላይ ያደረሰው ጉዳት አለመኖሩን አስታውቋል። በያዝነው ነሐሴ...
    0 Comments 0 Shares