በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የተከታታይ ትምህርት መርሃ-ግብሮች ትኩረት ሊደረግባቸው ይገባል ተባለ፡፡

0
0

ተከታታይ የትምህርት መርሃ-ግብር አያሌ ዜጐችን በማታ፣ በክረምትና በእረፍት ቀናት ተምረው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ላይ እንዲሰማሩ ማስቻሉ በጥናት ተደርሶበታል፡፡
ይሁን እንጂ የተከታታይ ትምህርት አሰጣጡና ተመራቂዎች ጥራትና ውጤታማነት ላይ የተለያዩ ጥያቄዎች ይነሣሉ፡፡

ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ከሆነ የተከታታይ ትምህርት መርሃ-ግብሮች ከትምህርት ተቋማቱ ጀምሮ በትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ በከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ የሚደረግላቸው ክትትል ዝቅተኛ ነው፡፡

የተከታታይ ትምህርት መርሃ-ግብሩን ጥራት ከሚፈታተኑት ውስጥ የትምህርት መስኮች አግባብ ያለው ጥናት ሳይደረግባቸው መከፈትና ለሚሰጡ ትምህርቶች በቂ መርጃ መሣሪያዎች አለመኖራቸው ነው፡፡

ለተከታታይ ትምህርት መርሃ-ግብሮች ደግሞ በአብዛኛው ከሚፈለገው ደረጃ በታች የሆኑና በትርፍ ጊዜ የሚሰሩ መምህራንን መድቦ ማሰተማር በዋናነት ጥራቱን ጥያቄ ውስጥ የሚከቱት መሆኑን ነው ጥናቶች የሚያስረዱት፡፡

የፈተናና የነጥብ ወይንም ማርክ አሰጣጥ ስርዓቱም የላላ ነው ተብሏል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያለው የትምህርት አሰጣጥ ጥራትን ለመቆጣጠር የሚያስችለውን መዋቅር አዘጋጅቶ ለትምህርት ሚኒስቴር ቢልክም ምላሹ እንደዘገየበት መናገሩን መዘገባችን ይታወሣል፡፡

የተከታታይ ትምህርት መርሃ ግብሩ በመደበኛው የትምህርት ጊዜ ለመማር እድል ያላገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ይታወቃል፡፡

(በየነ ወልዴ)sheger fm

Search
Categories
Read More
Uncategorized
የዚምባብዌ ጦር ገዢው ፓርቲ ላይ በሚደረገው ጣልቃ ገብነት ላይ ማስጠንቀቂያ ሰጠ
ብዙም ያልተለመደው የጣልቃ ገብነት ጉዳይ የተከሰተው ሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ ምክትላቸው ኤመርሰን ምናንጋግዋን ከስራ ካሰናበቱ በኋላ ነው። ከ90...
By Dawitda 2017-11-14 18:21:39 0 0
Uncategorized
ዳይ እየተሰዳደብን ...
«ዘውድአለም ታደሰ» ሰው ሁሉ የፖለቲካ ተንታኝ ሆኖልኛል። ጭራሽ እየሩሳሌምን ለእስራኤል አሳልፈን አንሰጥም! አንሰጥም!...
By Zewdalem 2017-12-07 12:34:35 0 0
Uncategorized
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመሠራረት ምን ይመሥላል?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና መሥሪያ ቤቱ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ የሆነ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አየር መንገድ ድርጅት ነው። አየር መንገዱ ከቀድሞው ትራንስ...
By Dawitda 2017-12-04 06:54:03 0 0
Uncategorized
የመጀምሪያዋ የኢትዮጵያ ዘመናዊ የጦር መርከብ ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም ከመያዟ በፊት P.C. 1616 ትባል ነበር። ይህች ዘመናዊ መርከብ ከአሜሪካን መንግስት በእርዳታ የተገኘች ነበረች።
1616 ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም እንዲወጣላት በማስፈለጉ በጊዜው የነበረውን ተጨባጭ ሁ...
By Dawitda 2017-12-16 09:06:27 0 0
Uncategorized
ኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን በመበደል ከዓለም ቀዳሚ ሃገራት አንዷ ነች ተባለ
ኢትዮጵያ ከቻይና በመቀጠል ከሶሪያ እኩል የኢንተርኔት እና የሞባይል ተጠቃሚዎች ላይ ገደቦችን በመጣል በዓለም ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች ሲል ፍሪደም ሃውስ...
By Seller 2017-11-16 11:27:06 0 0