• Share
    #ZiniQ
    Share #ZiniQ
    Like
    2
    0 Comments 1 Shares
  • በኢትዮጵያ የሚከበሩ በዓላትን ለመታደም ከውጪ የሚመጡ ጎብኝዎች ከመጡበት ዋናው የበዓል ስነ ስርዓት በተጨማሪ የሚዘጋጁ ልዩ ልዩ የባህል ዝግጅቶች የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ እያደረጋቸው መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ።

    ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሶስት ወራት ከ256 ሺህ በላይ የውጪ ሀገራት ጎብኝዎችን አስተናግዳ፥ ከ959 ሚሊየን በላይ የአሜሪካ ዶላር ገቢ አግኝታለች።

    ይህ የጎብኝዎች ቁጥር ከ2 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የስራ እድል የፈጠረ መሆኑን ከባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

    ከጉልበት ሰራተኞች እስከ ባለሀብቱ፣ ከትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እስከ አየር መንገድ የቱሪዝም ዘርፉ ከሚፈጥረው የስራ እድል ተጠቃሚዎች ናቸው።

    በታህሳስ ወር መጨረሻ የሚከበረው የገና በዓልን ጨምሮ በጥምቀት በዓል ላይ በርካታ የውጪ ሀገራት ጎብኝዎች ይታደማሉ።

    በዓላትን ምክንያት አድርገው ወደ ሀገር ከሚገቡ ጎብኝዎችም የቱሪዝም ዘርፉ የሚጠበቀውን ገቢ እንዲያስገኝ የሚያስችሉ ስራዎች በክልሎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስቴሩ ይገልጻል።

    የጥምቀት በዓል በድምቀት በሚከበርባት ጎንደር ዘንድሮ የጎብኝዎችን ቆይታ የሚያራዝሙ፥ አዳዲስ ባህላዊ ዝግጅቶችን ለማቅረብ ዝግጅት መጀመሩን የአማራ ክልል ቅርስ ጥበቃ ባልስጣን አስታውቋል።

    በባለስልጣኑ የቅርስ ጥበቃ እና ልማት ዳይሬክተር አቶ የሽዋስ ደሳለኝ ከባህል ሳምንት አውደ ርዕይና ባዛር በተጨማሪ የጥምቀት የቁንጅና ውድድር በማዘጋጀት የበዓሉን ባህላዊ ይዘት ለማጉላት ጥረት ይደረጋል ብለዋል።

    የጎብኝዎች ቁጥር እንዲጨምር እና ህብረተሰቡ ከዘርፉ የሚያገኘውን ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችሉ የመስህብ ስፍራዎችን የማስተዋወቅ ስራዎች በስፋት መሰራታቸውንም ተናግረዋል።

    ከዚህ አንጻርም ጎብኝዎች ለጉብኝት በሚሄዱባቸው ስፍራዎች ቆይታቸውን እንዲያራዝሙ የሚያደርጉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ነው የገለፁት።

    የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር በዓላትን ተከትሎ አውደ ርዕይ፣ የንግድ ትርኢትና ባዛር፣ የባህላዊ ሙዚቃ ዝግጅትና የባህል ሳምንት በሚል የጎብኝዎችን ቆይታ ለማራዘም የሚደረጉ ጥረቶች ሊበረታቱ ይገባቸዋል ይላል።

    በሚኒሰቴሩ የዓለም አቀፍና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ አባተ፥ ክልሎች የጎብኝዎችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም በሚያከናውኗቸው የፈጠራ ስራዎች የአካባቢውን ዜጎች ተጠቃሚነት በቀላሉ ማሳደግ ያስችላቸዋል ነው ያሉት።

    አቶ ገዛኸኝ በፈጠራ ስራዎቻቸው በቱሪዝም ዘርፉ ላይ ውጤት የሚያመጡ ክልሎች የሚበረታቱበት አሰራር እየታሰበ መሆኑንም ጠቁመዋል።

    በባህል ልማት እና በመስህብ መዳረሻዎች ላይ የሚሰሩ ስራዎች አጥጋቢ አለመሆናቸው የፈጠሩት ክፍተት፥ ሃገሪቱ ከቱሪዝም ዘርፉ እንዳትጠቀም እንዳደረጋት ይነገራል።

    በዓመቱ መጨረሻ ከቱሪዝም ዘርፉ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ለማግኘት የታቀደ ሲሆን፥ ሚኒስቴሩም የታቀደውን ገቢ ማግኘት እንዲቻል ዘላቂ የመሰረተ ልማት ግንባታ እና የመስህብ ስፍራዎች ጥበቃ ስራ ሊሰራ እንደሚገባ ይገልጻል።
    በኢትዮጵያ የሚከበሩ በዓላትን ለመታደም ከውጪ የሚመጡ ጎብኝዎች ከመጡበት ዋናው የበዓል ስነ ስርዓት በተጨማሪ የሚዘጋጁ ልዩ ልዩ የባህል ዝግጅቶች የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ እያደረጋቸው መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሶስት ወራት ከ256 ሺህ በላይ የውጪ ሀገራት ጎብኝዎችን አስተናግዳ፥ ከ959 ሚሊየን በላይ የአሜሪካ ዶላር ገቢ አግኝታለች። ይህ የጎብኝዎች ቁጥር ከ2 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የስራ እድል የፈጠረ መሆኑን ከባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል። ከጉልበት ሰራተኞች እስከ ባለሀብቱ፣ ከትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እስከ አየር መንገድ የቱሪዝም ዘርፉ ከሚፈጥረው የስራ እድል ተጠቃሚዎች ናቸው። በታህሳስ ወር መጨረሻ የሚከበረው የገና በዓልን ጨምሮ በጥምቀት በዓል ላይ በርካታ የውጪ ሀገራት ጎብኝዎች ይታደማሉ። በዓላትን ምክንያት አድርገው ወደ ሀገር ከሚገቡ ጎብኝዎችም የቱሪዝም ዘርፉ የሚጠበቀውን ገቢ እንዲያስገኝ የሚያስችሉ ስራዎች በክልሎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስቴሩ ይገልጻል። የጥምቀት በዓል በድምቀት በሚከበርባት ጎንደር ዘንድሮ የጎብኝዎችን ቆይታ የሚያራዝሙ፥ አዳዲስ ባህላዊ ዝግጅቶችን ለማቅረብ ዝግጅት መጀመሩን የአማራ ክልል ቅርስ ጥበቃ ባልስጣን አስታውቋል። በባለስልጣኑ የቅርስ ጥበቃ እና ልማት ዳይሬክተር አቶ የሽዋስ ደሳለኝ ከባህል ሳምንት አውደ ርዕይና ባዛር በተጨማሪ የጥምቀት የቁንጅና ውድድር በማዘጋጀት የበዓሉን ባህላዊ ይዘት ለማጉላት ጥረት ይደረጋል ብለዋል። የጎብኝዎች ቁጥር እንዲጨምር እና ህብረተሰቡ ከዘርፉ የሚያገኘውን ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችሉ የመስህብ ስፍራዎችን የማስተዋወቅ ስራዎች በስፋት መሰራታቸውንም ተናግረዋል። ከዚህ አንጻርም ጎብኝዎች ለጉብኝት በሚሄዱባቸው ስፍራዎች ቆይታቸውን እንዲያራዝሙ የሚያደርጉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ነው የገለፁት። የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር በዓላትን ተከትሎ አውደ ርዕይ፣ የንግድ ትርኢትና ባዛር፣ የባህላዊ ሙዚቃ ዝግጅትና የባህል ሳምንት በሚል የጎብኝዎችን ቆይታ ለማራዘም የሚደረጉ ጥረቶች ሊበረታቱ ይገባቸዋል ይላል። በሚኒሰቴሩ የዓለም አቀፍና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ አባተ፥ ክልሎች የጎብኝዎችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም በሚያከናውኗቸው የፈጠራ ስራዎች የአካባቢውን ዜጎች ተጠቃሚነት በቀላሉ ማሳደግ ያስችላቸዋል ነው ያሉት። አቶ ገዛኸኝ በፈጠራ ስራዎቻቸው በቱሪዝም ዘርፉ ላይ ውጤት የሚያመጡ ክልሎች የሚበረታቱበት አሰራር እየታሰበ መሆኑንም ጠቁመዋል። በባህል ልማት እና በመስህብ መዳረሻዎች ላይ የሚሰሩ ስራዎች አጥጋቢ አለመሆናቸው የፈጠሩት ክፍተት፥ ሃገሪቱ ከቱሪዝም ዘርፉ እንዳትጠቀም እንዳደረጋት ይነገራል። በዓመቱ መጨረሻ ከቱሪዝም ዘርፉ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ለማግኘት የታቀደ ሲሆን፥ ሚኒስቴሩም የታቀደውን ገቢ ማግኘት እንዲቻል ዘላቂ የመሰረተ ልማት ግንባታ እና የመስህብ ስፍራዎች ጥበቃ ስራ ሊሰራ እንደሚገባ ይገልጻል።
    0 Comments 0 Shares
  • Like
    1
    0 Comments 1 Shares
  • Like
    3
    0 Comments 0 Shares
  • Like
    2
    0 Comments 0 Shares
  • A girl in Bahir Dar, Ethiopia #united_nations_foundation #ethiopia #fighting_child_marriage #hunger_and_hope
    A girl attending a gathering in the rural village of Bahir Dar to discuss the positive benefits of a United Nations Foundation program that provides their families with a pregnant ewe in exchange for letting their daughters wait until their 18th birthday to decide on their own marriage options instead of being married off as young as eight years old. During this time the girls attend school, learn basic life skills, discover their rights, and so begin to fight the cycle of poverty and hunger.
    WHAT MAKES THIS PHOTO GREAT?
    A girl in Bahir Dar, Ethiopia #united_nations_foundation #ethiopia #fighting_child_marriage #hunger_and_hope A girl attending a gathering in the rural village of Bahir Dar to discuss the positive benefits of a United Nations Foundation program that provides their families with a pregnant ewe in exchange for letting their daughters wait until their 18th birthday to decide on their own marriage options instead of being married off as young as eight years old. During this time the girls attend school, learn basic life skills, discover their rights, and so begin to fight the cycle of poverty and hunger. WHAT MAKES THIS PHOTO GREAT?
    Like
    2
    0 Comments 1 Shares
  • በ270 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የሚተገበር የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሊዝ ፋይናንስ ፕሮጀክት ዛሬ ይፋ ተደርጓል።

    የኢንዱስትሪ ልማት ዘርፉ በሀገሪቱ ከሚፈጥረው ሰፊ የስራ እድል እና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ አቅም አንፃር የካፒታል እጥረት፣ የቴክኖሎጂ እና የንግድ ስራ እውቀት ውስንነት የዘርፉ ተግዳሮቶች ሆነው ቆይተዋል።

    መንግስት እነዚህን የዘርፉ ተግዳሮቶች ለመቅረፍ ሰፊ ስራ እየሰራ መሆኑን ቢገልፅም፥ ካለው ፍላጎት አንፃር ሰፊ ክፍተት እንዳለበት ነው በዘርፉ የተደረጉ ጥናቶች የሚያሳዩት።

    ዛሬ ይፋ የተደረገው የ270 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ፕሮጀክትም፥ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ ጉድለቶችን በመሙላት ለዘርፉ እንቅስቃሴ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ነው የተባለው።

    ፕሮጀክቱ አራት ምእራፎች ያሉት ሲሆን፥ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኩል የሚከናወን የ269 የአሜሪካ ዶላር በጀት ይኖረዋል።

    የንግድ ስራ አገልግሎቱ ደግሞ ለ912 ኢንተርፕራይዞች በፍላጎት ላይ የተመሰረተ ስልጠና ይሰጣል።

    ስራዉንም በፌዴራል አነስተኛ እና መካከለኛ የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች ልማት ኤጀንሲ ስር የተቋቋመው የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት የሚያከናውነው ሲሆን፥ ለዚህም 2 ነጥብ 5 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በጀት አለው።

    የኤጀንሲው ዋና ዳሬክተር አቶ አስፋው አበበ፥ ዛሬ ይፋ የተደረገው ፕሮጀክት ዋና አላማ በማሽን እጦት እና አቅም ውስንነት ምክንያት ወደ ማምረት ያልገቡ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ እንዲገቡ ክልሎችን ለማሳወቅ ነው ብለዋል።

    ዋና ዳሬክተሩ በዚህ ሊዝ ፋይናንስ ተጠቃሚ የሚሆኑት ዘርፎች መለየታቸውን አስረድተዋል።

    የሊዝ ፋይናንሱ ከአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በተጨማሪም በንግድ ፣ በአገልግሎት ዘርፍ ለተሰማሩ እና አርሶ አደሮች ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ተብሏል።

    ይህ ለአምስት ዓመት በሚቆየው ፕሮጀክት የሚገኘው ገንዘብ፥ 80 በመቶው ለማሽነሪዎች ግዢ፣ 20 በመቶው ደግሞ ለስራ ማስኬጃ የሚሆን የብድር አገልግሎት የሚውል ነው።

    ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኩል ለኢንተርፕራይዞች የሚቀርብ ሲሆን፥ ለተዘነጉ እና በኢኮኖሚ ውስጥ የሚሳተፉ ኢንተርፕራይዞችን በሁለት መልኩ ተጠቃሚ ያደርጋል ሲሉ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የውጭ ገንዘብ እና ብድር አስተዳደር ዳይሬክተር ዶክተር በሀይሉ ካሴ ገልፀዋል።

    ዶክተር በሀይሉ ኢንተርፕራይዞቹ የሊዝ ፋይናንስ ተጠቃሚ ሲሆኑ፥ እንደየ ፕሮጀክቱ የፋይናንስ እንቅስቃሴ የብድር አመላለሱ የሚወሰን ሆኖ እስከ ሰባት ዓመት የጊዜ ገደብ ይኖረዋል ነው ያሉት።

    ልማት ባንኩ በፕሮጀክቱ የተገኘውን ገንዘብ የማስተዳደር ስራ ከመስራት ባሻገር፥ በራሱ 12 ሚሊየን ዶላር ወጪ በማድረግ 36 ኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚ ማድረጉንም ነው ዳይሬክተሩ ያብራሩት።

    ለፕሮጀክቱ የሚውለው ገንዘብ በዓለም ባንክ ውስጥ ከሚገኘው የዓለም ልማት ማህበር እና ከአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የተገኘ ነው።
    በ270 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የሚተገበር የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሊዝ ፋይናንስ ፕሮጀክት ዛሬ ይፋ ተደርጓል። የኢንዱስትሪ ልማት ዘርፉ በሀገሪቱ ከሚፈጥረው ሰፊ የስራ እድል እና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ አቅም አንፃር የካፒታል እጥረት፣ የቴክኖሎጂ እና የንግድ ስራ እውቀት ውስንነት የዘርፉ ተግዳሮቶች ሆነው ቆይተዋል። መንግስት እነዚህን የዘርፉ ተግዳሮቶች ለመቅረፍ ሰፊ ስራ እየሰራ መሆኑን ቢገልፅም፥ ካለው ፍላጎት አንፃር ሰፊ ክፍተት እንዳለበት ነው በዘርፉ የተደረጉ ጥናቶች የሚያሳዩት። ዛሬ ይፋ የተደረገው የ270 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ፕሮጀክትም፥ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ ጉድለቶችን በመሙላት ለዘርፉ እንቅስቃሴ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ነው የተባለው። ፕሮጀክቱ አራት ምእራፎች ያሉት ሲሆን፥ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኩል የሚከናወን የ269 የአሜሪካ ዶላር በጀት ይኖረዋል። የንግድ ስራ አገልግሎቱ ደግሞ ለ912 ኢንተርፕራይዞች በፍላጎት ላይ የተመሰረተ ስልጠና ይሰጣል። ስራዉንም በፌዴራል አነስተኛ እና መካከለኛ የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች ልማት ኤጀንሲ ስር የተቋቋመው የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት የሚያከናውነው ሲሆን፥ ለዚህም 2 ነጥብ 5 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በጀት አለው። የኤጀንሲው ዋና ዳሬክተር አቶ አስፋው አበበ፥ ዛሬ ይፋ የተደረገው ፕሮጀክት ዋና አላማ በማሽን እጦት እና አቅም ውስንነት ምክንያት ወደ ማምረት ያልገቡ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ እንዲገቡ ክልሎችን ለማሳወቅ ነው ብለዋል። ዋና ዳሬክተሩ በዚህ ሊዝ ፋይናንስ ተጠቃሚ የሚሆኑት ዘርፎች መለየታቸውን አስረድተዋል። የሊዝ ፋይናንሱ ከአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በተጨማሪም በንግድ ፣ በአገልግሎት ዘርፍ ለተሰማሩ እና አርሶ አደሮች ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ተብሏል። ይህ ለአምስት ዓመት በሚቆየው ፕሮጀክት የሚገኘው ገንዘብ፥ 80 በመቶው ለማሽነሪዎች ግዢ፣ 20 በመቶው ደግሞ ለስራ ማስኬጃ የሚሆን የብድር አገልግሎት የሚውል ነው። ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኩል ለኢንተርፕራይዞች የሚቀርብ ሲሆን፥ ለተዘነጉ እና በኢኮኖሚ ውስጥ የሚሳተፉ ኢንተርፕራይዞችን በሁለት መልኩ ተጠቃሚ ያደርጋል ሲሉ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የውጭ ገንዘብ እና ብድር አስተዳደር ዳይሬክተር ዶክተር በሀይሉ ካሴ ገልፀዋል። ዶክተር በሀይሉ ኢንተርፕራይዞቹ የሊዝ ፋይናንስ ተጠቃሚ ሲሆኑ፥ እንደየ ፕሮጀክቱ የፋይናንስ እንቅስቃሴ የብድር አመላለሱ የሚወሰን ሆኖ እስከ ሰባት ዓመት የጊዜ ገደብ ይኖረዋል ነው ያሉት። ልማት ባንኩ በፕሮጀክቱ የተገኘውን ገንዘብ የማስተዳደር ስራ ከመስራት ባሻገር፥ በራሱ 12 ሚሊየን ዶላር ወጪ በማድረግ 36 ኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚ ማድረጉንም ነው ዳይሬክተሩ ያብራሩት። ለፕሮጀክቱ የሚውለው ገንዘብ በዓለም ባንክ ውስጥ ከሚገኘው የዓለም ልማት ማህበር እና ከአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የተገኘ ነው።
    0 Comments 0 Shares
  • ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትነት 22 ዕጩዎች ቀረቡ
    ከዕጩዎቹ መካከል የጠቅላይ ሚኒስትሩ ታናሽ ወንድም ይገኙበታል
    ለአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትነት 22 ዕጩዎች ቀረቡ፡፡ የዩኒቨርሲቲው የሕዝብ ግንኙነት ጽሕፈት ቤት በማኅበራዊ ሚዲያ ድረ ገጹ እንዳስታወቀው፣ ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ 22 ምሁራን ዩኒቨርሲቲውን በፕሬዚዳንትነት ለማገልግል በወጣው ማስታወቂያ መሠረት ማመልከቻቸውን አስገብተዋል፡፡

    ከእነዚህ አመልካቾች ውስጥ የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የወቅቱ ፕሬዚዳንትና የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ታናሽ ወንድም የ49 ዓመቱ ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ ይገኙበታል፡፡ ፕሮፌሰር ፍቅሬ ከአንድ ዓመት በፊት የሲቪል ሰርቪስ ፕሬዚዳንት በመሆን ተሹመው አሁንም እየሠሩ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

    አሁን እንደ አዲስ የተጀመረው የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶችን አወዳድሮ የመምረጥ ሥርዓት ከዚህ ቀደም ከነበረው አሠራር የተለየ ነው፡፡

    ከዚህ በፊት የዩኒቨርሲቲ ቦርድ በሥራ ላይ ባለው የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር 650/2001 መሠረት አወዳድሮ ከሚያቀርባቸው ዕጩዎች መካከል፣ እንደ አግባቡ በትምህርት ሚኒስትሩ ወይም በሚመለከተው የክልል ፕሬዚዳንቱ ይሾሙ ነበር፡፡ ከዚህ ዓመት ጀምሮ ግን ይኼ አሠራር ተቀይሯል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር በወጣው አዲስ መመርያ መሠረት ማንኛውም ለቦታው እመጥናለሁ የሚል ተወዳዳሪ፣ በዩኒቨርሲቲው በሚወጣው ክፍት የሥራ ማስታወቂያ መወዳደር ይችላል፡፡

    ይኼ አዲስ አሠራር ከተዋወቀ በኋላ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከወራት በፊት አዲስ ፕሬዚዳንት መሾሙ ይታወሳል፡፡ 60 ዓመታት ያስቆጠረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም በአዲሱ አሠራር መሠረት ፕሬዚዳንቱን በመሾም ሁለተኛ ይሆናል፡፡

    በ1950 የተመሠረተው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ ቀደም አሥር ፕሬዚዳንቶች የመሩት ሲሆን፣ ከ2003 ዓ.ም. እስከ 2010 ዓ.ም. ድረስ አድማሱ ፀጋዬ (ዶ/ር) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እንደነበሩ ይታወሳል፡፡

    ከአሁኑ የፕሬዚዳንት አሰያየም ጋር በተያያዘ ለ16 ቀናት እስከ ታኅሳስ 9 ቀን 2010 ዓ.ም. ድረስ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አመልካቾችን ሲቀበል ነበር፡፡ ካመለከቱት 22 ተወዳዳሪዎች ውስጥም 12 የሚሆኑት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ እየሠሩ ያሉ ምሁራን ናቸው፡፡ ቀሪዎቹ ከሌሎች ተቋማት፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ውጭ በሚገኙ የትምህርት ተቋማት የሚሠሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ዜጎች እንደሚገኙበት ማወቅ ተችሏል፡፡

    ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትነት 22 ዕጩዎች ቀረቡ ከዕጩዎቹ መካከል የጠቅላይ ሚኒስትሩ ታናሽ ወንድም ይገኙበታል ለአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትነት 22 ዕጩዎች ቀረቡ፡፡ የዩኒቨርሲቲው የሕዝብ ግንኙነት ጽሕፈት ቤት በማኅበራዊ ሚዲያ ድረ ገጹ እንዳስታወቀው፣ ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ 22 ምሁራን ዩኒቨርሲቲውን በፕሬዚዳንትነት ለማገልግል በወጣው ማስታወቂያ መሠረት ማመልከቻቸውን አስገብተዋል፡፡ ከእነዚህ አመልካቾች ውስጥ የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የወቅቱ ፕሬዚዳንትና የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ታናሽ ወንድም የ49 ዓመቱ ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ ይገኙበታል፡፡ ፕሮፌሰር ፍቅሬ ከአንድ ዓመት በፊት የሲቪል ሰርቪስ ፕሬዚዳንት በመሆን ተሹመው አሁንም እየሠሩ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ አሁን እንደ አዲስ የተጀመረው የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶችን አወዳድሮ የመምረጥ ሥርዓት ከዚህ ቀደም ከነበረው አሠራር የተለየ ነው፡፡ ከዚህ በፊት የዩኒቨርሲቲ ቦርድ በሥራ ላይ ባለው የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር 650/2001 መሠረት አወዳድሮ ከሚያቀርባቸው ዕጩዎች መካከል፣ እንደ አግባቡ በትምህርት ሚኒስትሩ ወይም በሚመለከተው የክልል ፕሬዚዳንቱ ይሾሙ ነበር፡፡ ከዚህ ዓመት ጀምሮ ግን ይኼ አሠራር ተቀይሯል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር በወጣው አዲስ መመርያ መሠረት ማንኛውም ለቦታው እመጥናለሁ የሚል ተወዳዳሪ፣ በዩኒቨርሲቲው በሚወጣው ክፍት የሥራ ማስታወቂያ መወዳደር ይችላል፡፡ ይኼ አዲስ አሠራር ከተዋወቀ በኋላ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከወራት በፊት አዲስ ፕሬዚዳንት መሾሙ ይታወሳል፡፡ 60 ዓመታት ያስቆጠረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም በአዲሱ አሠራር መሠረት ፕሬዚዳንቱን በመሾም ሁለተኛ ይሆናል፡፡ በ1950 የተመሠረተው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ ቀደም አሥር ፕሬዚዳንቶች የመሩት ሲሆን፣ ከ2003 ዓ.ም. እስከ 2010 ዓ.ም. ድረስ አድማሱ ፀጋዬ (ዶ/ር) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እንደነበሩ ይታወሳል፡፡ ከአሁኑ የፕሬዚዳንት አሰያየም ጋር በተያያዘ ለ16 ቀናት እስከ ታኅሳስ 9 ቀን 2010 ዓ.ም. ድረስ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አመልካቾችን ሲቀበል ነበር፡፡ ካመለከቱት 22 ተወዳዳሪዎች ውስጥም 12 የሚሆኑት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ እየሠሩ ያሉ ምሁራን ናቸው፡፡ ቀሪዎቹ ከሌሎች ተቋማት፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ውጭ በሚገኙ የትምህርት ተቋማት የሚሠሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ዜጎች እንደሚገኙበት ማወቅ ተችሏል፡፡
    0 Comments 0 Shares