• Meskel celebration in Addis Ababa, 1957.
    Source: Twitter.
    Meskel celebration in Addis Ababa, 1957. Source: Twitter.
    Like
    2
    0 Comments 0 Shares
  • ስትሮክ እየጨረሰን ነው

    (መላኩ ብርሃኑ)
    ……………………………………

    ይህንን መረጃ ሳነብ ያገኘሁት ነው። ለሁላችንም እንዲጠቅም ወደአማርኛ መልሼዋለሁ። ስትሮክ የዕለት ከዕለት ችግራችን እየሆነና የሁላችንንም ጓዳ እያንኳኳ በመሆኑ መረጃው ይጠቅመናል ብዬ አስባለሁ። እባካችሁ ሼር በማድረግ እውቀት አሸጋግሩ። ምናልባት በዚህ መረጃ የአንድ ሰው ህይወት ታተርፉ ይሆናል።

    እኔ በበኩሌ ከ8 አመት በፊት ይህ መረጃ ቢኖረኝ ኖሮ ምናልባት ወንድሜን ከሞት የማትረፍ እድል ይኖረኝ ነበር። እሁድ ቀን ጠዋት ነው። ወደጓደኛዬ ኒካ ስነስርአት ለመሄድ ስነሳ ወንድሜ ቀድሞኝ ከቤት ወጥቶ ስለነበር ከቤታችን ደጃፍ የሚገኝ አስፋልት መንገድ ዳር ላይ ተቀምጦ አይቼው ነበር። ከአይኑ እስክጠፋ ቁጭ ባለበት ቦታ ሆኖ ያየኝ እንደነበር ያወቅኩት ርቄ ሄጄ ዘወር ስል ወደኔ አቅጣጫ ያይ እንደነበር በመታዘቤ ነው።

    ከሁለት ሰአታት በኋላ ፑል በመጫወት ላይ እንዳለ ተዝለፍልፎ ወደቀ ተብሎ ተደወለልኝ። ስደርስ ቤተዛታ ሆስፒታል ገብቶ ስትሬቸር ላይ ተኝቶ አገኘሁት። ሃኪሞች ከሻይ እስኪመለሱ እርዳታ አላገኘም። ቀስ በቀስ ራሱን ሙሉ በሙሉ ሳተ። ችግሩ ምን እንደሆነ አላወቅንም የነገረንም ሃኪም የለም። በመጨረሻ ቤተዛታ ከአቅሜ በላይ ነው አልችልም አለ ……ጥቁር አንበሳ በበኩሉ አልጋ የለኝም ሲል…እኛም ለጭንቅላት ምርመራ የታዘዘልንን ኤምአርአይ ፍለጋ ስንንከራተት ሰአቱ ገፋ። መጨረሻ ላይ ሀያት ሆስፒታል አልጋ ተገኝቶ የፅኑ ህሙማን ጥብቅ ክትትል ክፍል (ICU) ገባ። በዚያው ሁኔታ ሳለ በሶስተኛው ቀን ህይወቱ አለፈ።ገና በ22 አመቱ። ለቤታችን ታላቅ ሃዘን ሆነ። ዛሬ ድረስ ሁኔታውን ሳስበው እንባዬን ማቆም አልችልም። እጅግ የምወደውን ወንድሜን የነጠቀኝ ስትሮክ ነው።

    ከዚያ ጊዜ በኋላ የቅርብ ዘመዶቼን ጨምሮ የማውቃቸው ብዙ ሰዎች በስትሮክ ተጠቅተው አይቻለሁ። ብዙዎቹ ሞተዋል።ብዙዎቹ ፓራላይዝ ሆነዋል። በዚህ ሁለት ወር ብቻ የማውቃቸው ሶስት ሰዎች በስትሮክ ሞተዋል።

    በስእሉ ላይ እንደምትመለከቱት ስትሮክ ወደአንጎል የሚሄደው ደምስር በረጋ ደም በሚዘጋበት ጊዜ የደም ዝውውር ሲቋረጥ የሚከሰት የደም ወደአንጎል መፍሰስ የሚያስከትለው ከባድ የጤና አደጋ ነው። ከባድ የደም ግፊት፣ የልብና ኩላሊት በሽታ ለስትሮክ መከሰት ዋና ምክንያቶች መሆናቸውን ሃኪሞች ይናገራሉ።

    ብዙዎቻችን ስለማናስተውለው እንጂ የምንሰማው የዘመድ ወዳጆቻችን ድንገተኛ ሞትና ራስ መሳት ከስትሮክ ጋር ቁርኝት አለው። ይህ አደጋ ድንገት ባልታሰበ ሰአት ይከሰታል። ተኝተን፣ እየሰራን፣ እየበላን፣ እየተጫወትን፣ መንገድ ላይ ሆነን ሊከሰትብን ይችላል።

    በስትሮክ የተመታ ሰው ለብዙ ጉዳቶች ሊዳረግ ይችላል። አንዳንዶችን በሙሉ ወይም በከፊል ፓራላይዝ ያደርጋል። አንዳንዶቹን የአእምሮ ማስታወስ ችሎታቸውን በሙሉ ወይም በከፊል ይነጥቃቸውና ሚስትና ልጆቻቸውን ጭምር እንዲረሱ ያደርጋቸዋል። የከፋ ጊዜ ልክ ኮምፒውተር ፎርማት እንደሚደረገው ሁሉ ስትሮክ ያጠቃቸውን ሰዎችም አዕምሯቸው ምንም ሳያስቀር ሙሉ በሙሉ የመርሳት ችግር ይጋርጥባቸዋል። አንዳንዶቹ ላይ ደሞ ራስን ስቶ ሽንትና ሰገራ ለመቆጣጠር እስካለመቻል ምግብ እስካለመቀበልና በመጨረሻም እስከሞት ያደርሳቸዋል።

    የስትሮክ የከፋው ጠባይ የያዘውን ሰው አንዳንዴ ከሞቱት በላይ ከቆሙት በታች አድርጎ ማስቀረቱ ነው። እናት ለታመመ ልጇ ሞትን እስክትመኝ የታመመ ሰው በጠያቂ "አሁንስ በገላገለው " እስከሚባል ድረስ ተስፋ ያስቆርጣል።

    የጭንቅላት ቀዶ ሃኪሞች አንዳንዴ ከተሳካላቸው በአንጎል ውስጥ የፈሰሰ ደምን በመጥረግ ህይወት ያተርፋሉ ወይም ጉዳት ይቀንሳሉ። በኛ አገር ደረጃ በከባድ ስትሮክ ተመትቶ ሙሉ በሙሉ የመዳን ብቻ ሳይሆን ከሞት የመትረፍ እድል ራሱ አናሳ ነው። እግዚአብሄር ተጨማሪ የመኖር እድል የሰጠው ሰው ከሳምንታት ወይም ወራት ራስን መሳት በኋላ ሙሉ በሙሉ ተርፎ በተአምር ከሞት ወደህይወት ይመለሳል። የአንዳንዱን ህይወት ደግሞ እስከእድሜ መጨረሻው ድረስ አበላሽቶ ያስቀረዋል። በአጠቃላይ ስትሮክ መቼና እንዴት እንደሚከሰት ስለማይታወቅ ሰይጣን በሽታ በሉት። ሹክክ ብሎ መጥቶ ውድ ህይወታችንን ይነጥቀናል።ወይም ከነበርንበት ሙሉነት ወደከባድ ጎዶሎነት ይቀይረናል።

    ስትሮክን በተመለከተ ያለው መልካም ዜና አንድ ብቻ ነው። ምልክቱን አውቀን ከቀደምነው የሞት በትሩን የማስጣል እድል አለን ። በጣም ቀላል በሆኑ ዘዴዎች አንድ ሰው በስትሮክ ስለመመታቱ ማረጋገጥና በፍጥነት ወደሀኪም ወስደን ህይወቱን ማትረፍ እንችላለን። በርግጥ እግዜር ይጠብቅ ነው እንጂ በኛ ሃገር ሃኪሞችና ሆስፒታል ሁኔታ ብዙ ተስፋ ማድረግ አይቻል ይሆናል። ( በወንድሜ ሞት ያረጋገጥኩት ይህንኑ ነው)። ነገር ግን ባለሙያዎች እንደሚያረጋግጡት የስትሮክ ምልክት የታየበት ሰው በ3ሰአታት ጊዜ ውስጥ ሃኪም ጋር ከደረሰ ሙሉ በሙሉ ለመዳን እድል አለው። ዋናው ጥያቄ አንድ ሰው በስትሮክ ሲመታ የሚያሳያቸው ምልክቶች ምንድናቸው? እንዴትስ ማወቅ ይቻላል? የሚለው ነው።

    አንዳንድ ጊዜ ምልክቶቹን ለመለየት ከባድ ቢሆንም STROKE አንድን ሰው እንዳጠቃው ለማወቅ የምንረዳባቸውን ቀላል ዘዴዎች አሉ። ቀዳሚው ዘዴ የ STROKE ን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ፊደላት በቃል ይዞ በአዕምሮ መመዝገብ ነው። STR

    S= smile. በትሮክ የተመታ ሰው ፈገግ ማለት ያዳግተዋል። ፊቱ ስሜት አልባ ይሆናል። አንድ ጊዜ ፈገግ እንዲል መጠየቅና ውጤቱን ማየት

    T =talk ስትሮክ አንደበት ስለሚይዝ የሚወጡ ቃላት እንዲንተባተቡና ትርጉመቢስ እንዲሆኑ ያደርጋል። ቀላል አረፍተነገርን ሳያቆራርጥ እንዲናገር መጠየቅ (ምሳሌ ቴሌቪዥኑን ስንት ትሸጠዋለህ? እንዲል )
    ውጤቱንም ማጤን

    R=raise hands ስትሮክ እጅና እግር እንዳይታዘዝ ያደርጋል። ሁለት እጆቹን ወደላይ እንዲያነሳ መጠየቅና ውጤቱን ማየት

    ከነዚህ አንዱን በትክክል መወጣት ከተሳነው የስትሮክ ምልክት ነውና ሃኪም ጋር በፍጥነት መውሰድ ጠቃሚ ይሆናል። በተጨማሪም ምላሱን ቀጥ አድርጎ እንዲያወጣ መጠየቅ ማውጣት ከተሳነው ወይም አጥፎና አጣሞ ካወጣው በስትሮክ የመመታት ምልክት ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል ።

    በቃ ይኸው ነው። ለሁሉም ሼር አድርገን ህይወት እናድን
    ስትሮክ እየጨረሰን ነው (መላኩ ብርሃኑ) …………………………………… ይህንን መረጃ ሳነብ ያገኘሁት ነው። ለሁላችንም እንዲጠቅም ወደአማርኛ መልሼዋለሁ። ስትሮክ የዕለት ከዕለት ችግራችን እየሆነና የሁላችንንም ጓዳ እያንኳኳ በመሆኑ መረጃው ይጠቅመናል ብዬ አስባለሁ። እባካችሁ ሼር በማድረግ እውቀት አሸጋግሩ። ምናልባት በዚህ መረጃ የአንድ ሰው ህይወት ታተርፉ ይሆናል። እኔ በበኩሌ ከ8 አመት በፊት ይህ መረጃ ቢኖረኝ ኖሮ ምናልባት ወንድሜን ከሞት የማትረፍ እድል ይኖረኝ ነበር። እሁድ ቀን ጠዋት ነው። ወደጓደኛዬ ኒካ ስነስርአት ለመሄድ ስነሳ ወንድሜ ቀድሞኝ ከቤት ወጥቶ ስለነበር ከቤታችን ደጃፍ የሚገኝ አስፋልት መንገድ ዳር ላይ ተቀምጦ አይቼው ነበር። ከአይኑ እስክጠፋ ቁጭ ባለበት ቦታ ሆኖ ያየኝ እንደነበር ያወቅኩት ርቄ ሄጄ ዘወር ስል ወደኔ አቅጣጫ ያይ እንደነበር በመታዘቤ ነው። ከሁለት ሰአታት በኋላ ፑል በመጫወት ላይ እንዳለ ተዝለፍልፎ ወደቀ ተብሎ ተደወለልኝ። ስደርስ ቤተዛታ ሆስፒታል ገብቶ ስትሬቸር ላይ ተኝቶ አገኘሁት። ሃኪሞች ከሻይ እስኪመለሱ እርዳታ አላገኘም። ቀስ በቀስ ራሱን ሙሉ በሙሉ ሳተ። ችግሩ ምን እንደሆነ አላወቅንም የነገረንም ሃኪም የለም። በመጨረሻ ቤተዛታ ከአቅሜ በላይ ነው አልችልም አለ ……ጥቁር አንበሳ በበኩሉ አልጋ የለኝም ሲል…እኛም ለጭንቅላት ምርመራ የታዘዘልንን ኤምአርአይ ፍለጋ ስንንከራተት ሰአቱ ገፋ። መጨረሻ ላይ ሀያት ሆስፒታል አልጋ ተገኝቶ የፅኑ ህሙማን ጥብቅ ክትትል ክፍል (ICU) ገባ። በዚያው ሁኔታ ሳለ በሶስተኛው ቀን ህይወቱ አለፈ።ገና በ22 አመቱ። ለቤታችን ታላቅ ሃዘን ሆነ። ዛሬ ድረስ ሁኔታውን ሳስበው እንባዬን ማቆም አልችልም። እጅግ የምወደውን ወንድሜን የነጠቀኝ ስትሮክ ነው። ከዚያ ጊዜ በኋላ የቅርብ ዘመዶቼን ጨምሮ የማውቃቸው ብዙ ሰዎች በስትሮክ ተጠቅተው አይቻለሁ። ብዙዎቹ ሞተዋል።ብዙዎቹ ፓራላይዝ ሆነዋል። በዚህ ሁለት ወር ብቻ የማውቃቸው ሶስት ሰዎች በስትሮክ ሞተዋል። በስእሉ ላይ እንደምትመለከቱት ስትሮክ ወደአንጎል የሚሄደው ደምስር በረጋ ደም በሚዘጋበት ጊዜ የደም ዝውውር ሲቋረጥ የሚከሰት የደም ወደአንጎል መፍሰስ የሚያስከትለው ከባድ የጤና አደጋ ነው። ከባድ የደም ግፊት፣ የልብና ኩላሊት በሽታ ለስትሮክ መከሰት ዋና ምክንያቶች መሆናቸውን ሃኪሞች ይናገራሉ። ብዙዎቻችን ስለማናስተውለው እንጂ የምንሰማው የዘመድ ወዳጆቻችን ድንገተኛ ሞትና ራስ መሳት ከስትሮክ ጋር ቁርኝት አለው። ይህ አደጋ ድንገት ባልታሰበ ሰአት ይከሰታል። ተኝተን፣ እየሰራን፣ እየበላን፣ እየተጫወትን፣ መንገድ ላይ ሆነን ሊከሰትብን ይችላል። በስትሮክ የተመታ ሰው ለብዙ ጉዳቶች ሊዳረግ ይችላል። አንዳንዶችን በሙሉ ወይም በከፊል ፓራላይዝ ያደርጋል። አንዳንዶቹን የአእምሮ ማስታወስ ችሎታቸውን በሙሉ ወይም በከፊል ይነጥቃቸውና ሚስትና ልጆቻቸውን ጭምር እንዲረሱ ያደርጋቸዋል። የከፋ ጊዜ ልክ ኮምፒውተር ፎርማት እንደሚደረገው ሁሉ ስትሮክ ያጠቃቸውን ሰዎችም አዕምሯቸው ምንም ሳያስቀር ሙሉ በሙሉ የመርሳት ችግር ይጋርጥባቸዋል። አንዳንዶቹ ላይ ደሞ ራስን ስቶ ሽንትና ሰገራ ለመቆጣጠር እስካለመቻል ምግብ እስካለመቀበልና በመጨረሻም እስከሞት ያደርሳቸዋል። የስትሮክ የከፋው ጠባይ የያዘውን ሰው አንዳንዴ ከሞቱት በላይ ከቆሙት በታች አድርጎ ማስቀረቱ ነው። እናት ለታመመ ልጇ ሞትን እስክትመኝ የታመመ ሰው በጠያቂ "አሁንስ በገላገለው " እስከሚባል ድረስ ተስፋ ያስቆርጣል። የጭንቅላት ቀዶ ሃኪሞች አንዳንዴ ከተሳካላቸው በአንጎል ውስጥ የፈሰሰ ደምን በመጥረግ ህይወት ያተርፋሉ ወይም ጉዳት ይቀንሳሉ። በኛ አገር ደረጃ በከባድ ስትሮክ ተመትቶ ሙሉ በሙሉ የመዳን ብቻ ሳይሆን ከሞት የመትረፍ እድል ራሱ አናሳ ነው። እግዚአብሄር ተጨማሪ የመኖር እድል የሰጠው ሰው ከሳምንታት ወይም ወራት ራስን መሳት በኋላ ሙሉ በሙሉ ተርፎ በተአምር ከሞት ወደህይወት ይመለሳል። የአንዳንዱን ህይወት ደግሞ እስከእድሜ መጨረሻው ድረስ አበላሽቶ ያስቀረዋል። በአጠቃላይ ስትሮክ መቼና እንዴት እንደሚከሰት ስለማይታወቅ ሰይጣን በሽታ በሉት። ሹክክ ብሎ መጥቶ ውድ ህይወታችንን ይነጥቀናል።ወይም ከነበርንበት ሙሉነት ወደከባድ ጎዶሎነት ይቀይረናል። ስትሮክን በተመለከተ ያለው መልካም ዜና አንድ ብቻ ነው። ምልክቱን አውቀን ከቀደምነው የሞት በትሩን የማስጣል እድል አለን ። በጣም ቀላል በሆኑ ዘዴዎች አንድ ሰው በስትሮክ ስለመመታቱ ማረጋገጥና በፍጥነት ወደሀኪም ወስደን ህይወቱን ማትረፍ እንችላለን። በርግጥ እግዜር ይጠብቅ ነው እንጂ በኛ ሃገር ሃኪሞችና ሆስፒታል ሁኔታ ብዙ ተስፋ ማድረግ አይቻል ይሆናል። ( በወንድሜ ሞት ያረጋገጥኩት ይህንኑ ነው)። ነገር ግን ባለሙያዎች እንደሚያረጋግጡት የስትሮክ ምልክት የታየበት ሰው በ3ሰአታት ጊዜ ውስጥ ሃኪም ጋር ከደረሰ ሙሉ በሙሉ ለመዳን እድል አለው። ዋናው ጥያቄ አንድ ሰው በስትሮክ ሲመታ የሚያሳያቸው ምልክቶች ምንድናቸው? እንዴትስ ማወቅ ይቻላል? የሚለው ነው። አንዳንድ ጊዜ ምልክቶቹን ለመለየት ከባድ ቢሆንም STROKE አንድን ሰው እንዳጠቃው ለማወቅ የምንረዳባቸውን ቀላል ዘዴዎች አሉ። ቀዳሚው ዘዴ የ STROKE ን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ፊደላት በቃል ይዞ በአዕምሮ መመዝገብ ነው። STR S= smile. በትሮክ የተመታ ሰው ፈገግ ማለት ያዳግተዋል። ፊቱ ስሜት አልባ ይሆናል። አንድ ጊዜ ፈገግ እንዲል መጠየቅና ውጤቱን ማየት T =talk ስትሮክ አንደበት ስለሚይዝ የሚወጡ ቃላት እንዲንተባተቡና ትርጉመቢስ እንዲሆኑ ያደርጋል። ቀላል አረፍተነገርን ሳያቆራርጥ እንዲናገር መጠየቅ (ምሳሌ ቴሌቪዥኑን ስንት ትሸጠዋለህ? እንዲል ) ውጤቱንም ማጤን R=raise hands ስትሮክ እጅና እግር እንዳይታዘዝ ያደርጋል። ሁለት እጆቹን ወደላይ እንዲያነሳ መጠየቅና ውጤቱን ማየት ከነዚህ አንዱን በትክክል መወጣት ከተሳነው የስትሮክ ምልክት ነውና ሃኪም ጋር በፍጥነት መውሰድ ጠቃሚ ይሆናል። በተጨማሪም ምላሱን ቀጥ አድርጎ እንዲያወጣ መጠየቅ ማውጣት ከተሳነው ወይም አጥፎና አጣሞ ካወጣው በስትሮክ የመመታት ምልክት ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል ። በቃ ይኸው ነው። ለሁሉም ሼር አድርገን ህይወት እናድን
    0 Comments 1 Shares
  • ለሰውነታችን የሚያስፈልጉ ሜኔራሎች እነማን ናቸው?
    (በዳንኤል አማረ @ኢትዮጤና) #EthioTena #Minerals
    ✔ባዮቲን!
    ባዮቲን ነርቮችን፣ ቆዳን እና የምግብ መፈጨት ስርዓትን ያግዛል። ለአዋቂ ወንድ እና ለሴቶች 30 ማይክሮ ግራም በቀን ያስፈልገናል። ሩብ ኩባያ ለውዝ 88% የባዮቲን የቀን ፍላጐታችንን ያሟል።
    ✔ካልሲየም!
    ካልሲየም ለአጥንት እና ጥርስ ጥንካሬ ጠቃሚ የመሰረት ድንጋይ ሜኔራል ነው። በተጨማሪም ጡንቻ እና ነርቭ ተግባራቸውን እንዲወጡ አስተዋጽዎ ያደርጋል። አዋቂ ወንዶችና ሴቶች 800 ሚ.ግ. ካልሲየም ያስፈልጋቸዋል። አንድ ኩባያ እርጐ 30% የካልሲየም የቀን ፍላጐታችንን ያሟላል።
    ✔ክሎሪን!
    ክሎሪን የነርቭ ስርዓታችንን በማገዝ እና የሴል ሜምብሬን አቋም ጤናማ እንዲሆን ያደርጋል። ለወንዶች 550 ሚ.ግ. ለሴቶች 425 ሚ.ግ. ክሎሪን በቀን ያስፈልጋል።አስር እግር ያለው ባለቅርፊት አሳ 36% የቀን ክሎሪን ፍላጐታችንን ያቀርባል።
    ✔ክሮሚየም!
    ክሮሚየም ፋትን፣ ፕሮቲን፣ እና ካርቦሃይድሬት ለመፍጨት ያገለግላል። 35 ማይክሮግራም በቀን ያስፈልገናል ሴቶች 25 ማይክሮ ግራም ያስፈልጋቸዋል። ግማሽ ኩባያ ብርኮሊ 11 ማይክሮ ግራም ክሮሚየም ይሰጠናል።
    ✔ኮፐር!
    ኮፐር አጥንት እና የተለያየ የሰውነት ክፍላችን ተቀናጅተው እንዲሰሩ ያደርጋቸዋል በተጨማሪም ሀይል/ጉልበት ይሰጣቸዋል። 700 በቀን ለወንድ እና ሴት ያስፈልጋቸዋል።
    ✔ፍሎራይድ!
    ፍሎራይድ ጥርስ እንዳይጐዳ ይከላከላል ጤናማ የሆነ አጥንት ለመገንባት ይጠቅማል። ከ0.1-0.5 ሚ.ግ. ለህፃናት፣ 4 ሚ.ግ. ለአዋቂ ወንድ 3 ሚ.ግ. ለአዋቂ ሴቶች በቀን ያስፈልጋቸዋል። አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ከመጠጥ ውሃ የፍሎራይድ ፍላጐታችንን እናሟላለን።
    ✔ፎሌት!
    ፎሌት የደም ሴሎቻችን እንዲመረቱ ለማድረግ ይጠቅማል በተለይ ለእርጉዝ ሴቶች ይጠቅማል። 300 ዮጂኤስ ለሴቶችን ወንዶች በቀን ያስፈልጋል። አንድ ኩባያ ምስር 90% የፎሌት ፍላጐታችንን ያሟላል።
    ✔አዮዲን!
    አዮዲን ጤናማ የታይሮይድ ሆርሞን እንዲመረት ያደርጋል። 95 ዮጂኤስ በቀን ለወንድ እና ሴቶች ያስፈልጋል። ስካሎፕ 90% የቀን ፍላጐታችንን ያሟላል።
    ✔ብረት(IRON)!
    ብረት (Iron) ኦክስጂን ወደተለያየ የሰውነት ክፍል ወስጥ እንዲሰራጭ ያደርጋል በተጨማሪም ሀይል/ጉልበት እንዲመረት ድጋፍ ያደርጋል። 6 ሚ.ግ. ለወንድ 8.1 ሚ.ግ. ለሴቶች በቀን ያስፈልጋል። አንድ ኩባያ ስፒናች (አረንጓዴ የሚበላ ቅጠል) 36% የቀን ፍላጐታችንን ያሟላል።
    ✔ማንጋኒዝ!
    ማንጋኒዝ ለቆዳ ጤንነት፣ ጐጂ አንቲኦክሲዳንት በመከላከል፣ ጤናማ የስኳር መጠን እንዲኖረን በማድረግ ይጠቅመናል። 2-5 ሚ.ግ. በቀን ለአዋቂዎች ያስፈልጋቸዋል። አንድ ኩባያ ቡናማ ሩዝ 88% የማንጋኒዝ ፍላጐታችንን ያሟላል።
    ✔ማግኒዚየም!
    ማግኒዚየም ሰውነታችን ጉልበት/ሀይል እንዲያመነጭ ያደርጋል፣ የነርቭ ስርዓታችንን ያመጣጥናል፣ የሰውነት መቆጣትን ይቆጣጠራል፣ የደም ስኳር መጠንን ይቆጣጠራል። 350 ሚ.ግ. ለወንዶች 265 ሚ.ግ. ለሴቶች በቀን ያስፈልጋል። ሩብ ኩባያ የድባ ፍሬ 48% የማግኒዚየም የቀን ፍላጐታችንን ያሟላል።
    ✔ኒያሲን!
    ኒያሲን ጉልበት/ሀይል ለማምረት ጠቃሚ ነው ጐጂ አንቲኦክሲዳንቶችን በመከላከል በሽታ እንዳይከሰት ያደርጋል። 12 ሚ.ግ. ለወንድ 11 ሚ.ግ. ለሴቶች በቀን ያስፈልጋል። የዶሮ ስጋ 97% የቀን ፍጆታችንን ያበረክታል።
    መልካም ጤንነት!!!
    ለሰውነታችን የሚያስፈልጉ ሜኔራሎች እነማን ናቸው? (በዳንኤል አማረ @ኢትዮጤና) #EthioTena #Minerals ✔ባዮቲን! ባዮቲን ነርቮችን፣ ቆዳን እና የምግብ መፈጨት ስርዓትን ያግዛል። ለአዋቂ ወንድ እና ለሴቶች 30 ማይክሮ ግራም በቀን ያስፈልገናል። ሩብ ኩባያ ለውዝ 88% የባዮቲን የቀን ፍላጐታችንን ያሟል። ✔ካልሲየም! ካልሲየም ለአጥንት እና ጥርስ ጥንካሬ ጠቃሚ የመሰረት ድንጋይ ሜኔራል ነው። በተጨማሪም ጡንቻ እና ነርቭ ተግባራቸውን እንዲወጡ አስተዋጽዎ ያደርጋል። አዋቂ ወንዶችና ሴቶች 800 ሚ.ግ. ካልሲየም ያስፈልጋቸዋል። አንድ ኩባያ እርጐ 30% የካልሲየም የቀን ፍላጐታችንን ያሟላል። ✔ክሎሪን! ክሎሪን የነርቭ ስርዓታችንን በማገዝ እና የሴል ሜምብሬን አቋም ጤናማ እንዲሆን ያደርጋል። ለወንዶች 550 ሚ.ግ. ለሴቶች 425 ሚ.ግ. ክሎሪን በቀን ያስፈልጋል።አስር እግር ያለው ባለቅርፊት አሳ 36% የቀን ክሎሪን ፍላጐታችንን ያቀርባል። ✔ክሮሚየም! ክሮሚየም ፋትን፣ ፕሮቲን፣ እና ካርቦሃይድሬት ለመፍጨት ያገለግላል። 35 ማይክሮግራም በቀን ያስፈልገናል ሴቶች 25 ማይክሮ ግራም ያስፈልጋቸዋል። ግማሽ ኩባያ ብርኮሊ 11 ማይክሮ ግራም ክሮሚየም ይሰጠናል። ✔ኮፐር! ኮፐር አጥንት እና የተለያየ የሰውነት ክፍላችን ተቀናጅተው እንዲሰሩ ያደርጋቸዋል በተጨማሪም ሀይል/ጉልበት ይሰጣቸዋል። 700 በቀን ለወንድ እና ሴት ያስፈልጋቸዋል። ✔ፍሎራይድ! ፍሎራይድ ጥርስ እንዳይጐዳ ይከላከላል ጤናማ የሆነ አጥንት ለመገንባት ይጠቅማል። ከ0.1-0.5 ሚ.ግ. ለህፃናት፣ 4 ሚ.ግ. ለአዋቂ ወንድ 3 ሚ.ግ. ለአዋቂ ሴቶች በቀን ያስፈልጋቸዋል። አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ከመጠጥ ውሃ የፍሎራይድ ፍላጐታችንን እናሟላለን። ✔ፎሌት! ፎሌት የደም ሴሎቻችን እንዲመረቱ ለማድረግ ይጠቅማል በተለይ ለእርጉዝ ሴቶች ይጠቅማል። 300 ዮጂኤስ ለሴቶችን ወንዶች በቀን ያስፈልጋል። አንድ ኩባያ ምስር 90% የፎሌት ፍላጐታችንን ያሟላል። ✔አዮዲን! አዮዲን ጤናማ የታይሮይድ ሆርሞን እንዲመረት ያደርጋል። 95 ዮጂኤስ በቀን ለወንድ እና ሴቶች ያስፈልጋል። ስካሎፕ 90% የቀን ፍላጐታችንን ያሟላል። ✔ብረት(IRON)! ብረት (Iron) ኦክስጂን ወደተለያየ የሰውነት ክፍል ወስጥ እንዲሰራጭ ያደርጋል በተጨማሪም ሀይል/ጉልበት እንዲመረት ድጋፍ ያደርጋል። 6 ሚ.ግ. ለወንድ 8.1 ሚ.ግ. ለሴቶች በቀን ያስፈልጋል። አንድ ኩባያ ስፒናች (አረንጓዴ የሚበላ ቅጠል) 36% የቀን ፍላጐታችንን ያሟላል። ✔ማንጋኒዝ! ማንጋኒዝ ለቆዳ ጤንነት፣ ጐጂ አንቲኦክሲዳንት በመከላከል፣ ጤናማ የስኳር መጠን እንዲኖረን በማድረግ ይጠቅመናል። 2-5 ሚ.ግ. በቀን ለአዋቂዎች ያስፈልጋቸዋል። አንድ ኩባያ ቡናማ ሩዝ 88% የማንጋኒዝ ፍላጐታችንን ያሟላል። ✔ማግኒዚየም! ማግኒዚየም ሰውነታችን ጉልበት/ሀይል እንዲያመነጭ ያደርጋል፣ የነርቭ ስርዓታችንን ያመጣጥናል፣ የሰውነት መቆጣትን ይቆጣጠራል፣ የደም ስኳር መጠንን ይቆጣጠራል። 350 ሚ.ግ. ለወንዶች 265 ሚ.ግ. ለሴቶች በቀን ያስፈልጋል። ሩብ ኩባያ የድባ ፍሬ 48% የማግኒዚየም የቀን ፍላጐታችንን ያሟላል። ✔ኒያሲን! ኒያሲን ጉልበት/ሀይል ለማምረት ጠቃሚ ነው ጐጂ አንቲኦክሲዳንቶችን በመከላከል በሽታ እንዳይከሰት ያደርጋል። 12 ሚ.ግ. ለወንድ 11 ሚ.ግ. ለሴቶች በቀን ያስፈልጋል። የዶሮ ስጋ 97% የቀን ፍጆታችንን ያበረክታል። መልካም ጤንነት!!!
    0 Comments 0 Shares
  • እንግዳ እና ‘ሬድ ሌብል’
    ኤፍሬም እንዳለ
    እንዴት ሰነበታችሁሳ!
    ስሙኝማ…አንድ የምናውቀው ሰው እቤቱ የዘመድ እንግዶች ድንገት ይመጡበታል። እንዳጋጣሚ ሆኖ ከተገናኙ ረጅም ጊዜ ነበር። ቀድመው ሳይደውሉ ወይም በሌላ መንገድ እንዲያውቅ ሳያደርጉት አንድ እሁድ ቀን ‘ከች’ ይላሉ፡፡ እሱ ደግሞ ኑሮ ትንሽ ጠመም ብሎበት ከሚስቱ ጋር ጀርባ አዙረው መተኛት ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ ቂ…ቂ…ቂ…(በኑሮም ቅጣት፣ ‘በዛም’ ቅጣት!) ደግሞላችሁ…“ከሬድ ሌብል፣ ከኋይት ሆርስ፣ ከቆርቆሮ ቢራ የትኛው ይሻልሀል?” ብሎ ልግስና ቀርቷል።
    እናማ… ሚስቱ ወጣ ትልና ከእንትና ሱቅ በዱቤ ለስላሳ ምናምን ገዛዝታ ትመጣለች፡፡ ምን ቢሆን ጥሩ ነው…የእንግዶቹ ፊት ‘አሸቦ’ መሰለላችሁ። ውስኪውስ? ቆርቆሮ ቢራውስ! “ይሄ ጥሬ ሥጋ ሙልጭ ብሎ ካላለቀማ መጣላታችን ነው!” የሚባለው ያዙኝ፣ ልቀቁኝ ግብዣውስ! ‘እንግዶቹ’ በስንት ጊዜያቸው እግር ጥሏቸው ቢመጡ… የለመዱትን ውስኪና ጥሬ ሥጋ ስላላገኙ…እንዳኮረፉ ተቀምጠው፣ እንዳኮረፉ ሄዱና አረፉት፡፡
    እኔ የምለው… ጊዜ እኮ ተለውጧል! ባለ ሸላይ መኪና እንደበዛው ሁሉ ባለጠማማ ጫማዎችም በዝተናል እኮ! በዕቃ ብዛት ‘ጧ’ ሊሉ የደረሱ የኮንዶሚንየም አንድ ክፍል ስቱዲዮ የሚያካክሉ ‘ፍሪጆች’ እንደበዙ ሁሉ፣ ሦስት ድስት አጣበው ሊይዙ የሚችሉ፣ አሁን ግን ነፋስ ሞልቶ የተረፋቸው ‘ፍሪጆች’ በዝተዋል እኮ! እናማ እንኳን ጥሬ ሥጋ ሊያቀርብ ሚስቱ የባልነት መብቱ ላይ እንኳን ማዕቀብ ጥላበት ይታዘንለታል እንጂ ይኮረፋል! ቂ…ቂ…ቂ…
    ስሙኝማ...እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ… የምር ግን ዘንድሮ ‘እንግዳ ማስተናገድ’ አስቸጋሪ እየሆነ ነው፡፡ በገንዘብ ችግር የጤፍ ፍጆታውን ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሀምሳ በመቶ የቀነሰው ሰውዬ እንዴት ነው ብላክ ሌብል ውስኪ፡ ዊንተር ምናምን ቮድካ ሊያቀርብልን የምንጠብቀው! ዘንድሮ አሥራ ምናምን ብር የገባች ስኒ ሻይም ከቀረበ ትልቅ ነገር ነው፡፡
    ደግሞላችሁ…በፊት ከዘመድ ወይም ከጓደኛ ‘እንግዳ’ ጋር እንደ ልባችን እናወራ ነበር፡፡ አለ አይደል …
    “ምን ይለኛል?”
    “ደግሞ ቀድታኝ ሄዳ ለማን እንደምትናገር ማን ያውቃል!”
    “እንዲህ አለች ብላ ከሰው ብታቆራርጠኝስ!”
    “‘እናንተን አይወዳችሁም ብሎ ቢያስጠቁረኝስ!” (ቂ…ቂ…ቂ… ልጄ ዘንድሮ ‘መጥላት’ ብቻ ሳይሆን ‘አለመውደድም’… ‘ጥርስ የሚያስነክስበት’ ዘመን ሆኗል።)
    አይነት ስጋቶች የሉብንም ነበር፡፡ መቀለድ ብንፈልግም ለሳቅ ያልነው ዞሮ እኛ የምንሳቀቅበት ይሆናል የሚል ስጋት አልነበረንም፡፡
    ዘንድሮ ሁሉም ተለውጧል፡፡ እና በፊት ‘የኩሼ’ ቤት ወሬ እንኳ ሳንደባበቅ እናወራው የነበረውን ሰው “ከእንትን ፋብሪካ የገዛሁት አንሶላ እንደተመቸኝ ነገር…” ብንለው… የሆነ ‘ቡድን ውስጥ ልንከተት’ እንችላላን፡፡ (ሰው በሚጠጣው ቢራ ‘የእንትን ቡድን አባል’ የሚባልበት ዘመን! “ስንት ባንክ እያለ አንተ እዛ ባንክ ምን ወሰደህ!” የሚባልበት ዘመን!)
    ደግሞላችሁ…የሆነ ‘የዘመድ እንግዳ’ ይመጣል፡፡ እንዴት ናችሁ ምናምን አይነት ልውውጥ ይካሄዳል።
    “ባለቤትህ ደህና ነች?”
    “ደህና ነች፡፡”
    “ምነው፣ የለችም እንዴ?“
    “አክስቷ ታመው ወደ አስኮ አካባቢ ሄዳለች…” ትላላችሁ፡፡ ዘመዶች ለጥቂት ጊዜ ዝም ይላሉ፡፡ ከዛም…
    “አክስቷ ሞታለች አልተባለም እንዴ?”
    “ይቺኛዋ በአባት በኩል ያለችው ነች፡፡”
    “ነ…ው!” የድምጹ ቃና “ድንቄም አክስት!” አይነት ነው፡፡ “ዘንድሮ አክስቴ አጎቴ እያሉ የሚሄዱ ሚስቶች ምንም ደስ አይሉኝም” ይባላል፡፡
    እኔ የምለው…በአክስትና ለቅሶ ቤት ለሰልስት በማደር ማሳበብ ቀርቷል እኮ! ዘንድሮ ‘ሌላ ነገር ቢያስቡ’ እንኳን ምን ሰበብ ያስፈልጋል፡፡ “ጉዳይ አለኝ፣ ማታ ትንሽ እቆያለሁ…” ማለት በቂ ነው። እናማ… በሰላም የተቀመጠውን ሰው ‘የዘመድ እንግዶች’ ሚስቱን እንዲጠረጥር ሊያደርጉት ይሞክራሉ፡፡
    ከሆኑ ሰዎች ጋር ሰብስብ ብላችሁ ባላችሁበት የድሮ ትምህርት ቤት ጓደኛ ይመጣል፡፡
    “አጅሬው፤ አንተ እኮ ድሮም ቢሆን የዋዛ አልነበርክም፣፡”
    ስሙኝማ...አንዳንዴ የድሮ ጓደኛ ችግሩ ምን መሰላችሁ…ጨዋታ ያሳመረ ይመስለውና…በቃ፣ ኤድዋርድ ስኖውደን ሆኖ ቁጭ! ስንት ዘመን ሁሉ ከአገር ምስጢርነት ባልተናነሰ ስትጠብቁት የኖራችሁትን ሁሉ…አለ አይደል…አውላላ ሜዳ ላይ ያሰጣዋል ነው የምላችሁ።
    “ስማ..ያኔ ዘጠነኛ ክፍል ሳለን…ትዝ ይልሀል…አስረኛ ዲ ክፍል ጓሮ…” ብሎ ‘መቀባጠር’ ሲጀምር…ፈጠን ብላችሁ
    “አዎ… ጊዜ ይሮጣል አይደል!” ምናምን ትላላችሁ። ከዛም… “አንተ ግን የት ጠፍተህ ነው የከረምከው! ከተገናኘን ቆየን እኮ…” ድንበር ዙሪያ ግንብ መገንባት በሉት፡፡ ዝም ብሎ ከለፈለፈ ሁሉም ነገር በማግስቱ ጠዋት መብራት ባለበትም፣ መብራት በጠፋበትም (‘አብዛኛውን ቦታ’ ለማለት ያህል!) ሁሉ ይዛመትላችኋል። እሱዬው ግን የተቦተረፈ የጤፍ ጆንያ ምናምን ነገር ይሆንላችኋል፡፡
    “ስማ እሷ ልጅ አለች እንዴ…”
    ሰውዬው አሞታል እንዴ!
    “እኔ እንጃ፣ የስንት ዘመን ወሬ ነው የምታወራው…” ስንት ነገር ተቀይሯል፡፡ ጭቃ ሹሞች ተለውጠዋል፣ ሚሌኒየሙ ተለውጧል፣ የእንትናዬዎች የዳሌ ቅርጽ ተለውጧል! እሱ የድሮ አስረኛ ዲ ክፍል ጓሮ ወሬ ያወራል!
    ይሄኔ የሆነ ሰው የኮረኮረው ይመስል ከት ብሎ ይስቃል፡፡
    “ስማ…እኔ እኮ እስካሁን የማልረሳው ከንፈሯ እንደዛ የተፈነከተ ሀብ፣ ሀብ የመሰለው እንዴት አድርገህ ብትስማት ነው!…ቦይ ፍሬንዷ ሰምቶ ብረት ቦክስ ይዞ የመጣው ትዝ አይልህም!”
    ይሄኔ በቃ ኩላሊት፣ ጉበት ምናምን ቦታ ሲለዋወጡ ይታወቃችኋል፡፡ እንደ ምሳሌ የምትታዩትን ሰው!
    “ምን አይነት የተባረከ ቤተሰብ ውስጥ ነው ያደገው…” የምትባሉትን ሰው!
    “ሰው ቀና ብሎ አያይም፣ እንዴት አይነት የተባረከ ሰው መሰላችሁ!” የምትባሉትን ሰው!
    “ቁመቱ ባያጥር ኖሮ (ቂ…ቂ…ቂ…) ልጄን ከአራት ልጆቿ አባት አፋትቼ እድርለት ነበር…” የምትባሉትን ሰው!
    ደግሞላችሁ የዘመድ እንግዶች አሉላችሁ፡፡ የሆኑ የሥራ ባልደረባችሁ፣ ወይም የኮንዶሚኒየም ጎረቤት፡ (ይቅርታ…ከጎን ያለ በሩ ሁልጊዜ የሚዘጋ ቤት እንጂ ለካስ የኮንዶሚኒየም ጎረቤት የለም…) ብቻ የሆኑ ሰዎች አብረዋችሁ አሉ፡፡ እና አንዷ ‘ዘመድ’…
    “አንተ በቃ እምቢ አልክ አይደል…” ትላለች፡፡ የምን ነገር! በቃ… ‘ፈንጂ ወረዳው’ ፊታችሁ መጥቶ ድቅን፡፡
    በኮንዶሚኒየሙ ‘ከጎናችሁ ወደሚኖረው’ ሰው ዘወር ብላችሁ…
    “የውሀውን ጉልበት ለምንድነው የማይጨመሩልን! እኔ’ጋ እኮ ብታያት እንደ ዓይን ጠብታ ነው የምትወርደው።”
    ‘ዘመድ’ ትቀጠላለች፡፡ ‘ምልክቱ’ አልገባትማ!
    “ያቺን የመሰለች ልጅ አግባ ስትባል እምቢ ብለህ አሁን ብታያት እንዴት አይነት ሴት ወይዘሮ መስላለች…ስንትከረፈፍ አመለጠችህ…”
    ሌላኛዋ ‘ዘመድ’ ትቀጥላለች…
    “እሱ እባክሽ ሲነግሩት መች ይሰማል..ድሮስ እንዴት ያስቸግረን እንደነበር አታስታውሺም!...” (ይሳሰቃሉ)
    የመጀመሪያዋ ትቀጥላላች…
    “እሱንማ ተዪው… ጎጃም በረንዳ እየሄደ አረቄውን ላይ በላይ መገልበጥ ለምዶ መለኪያዋን አክሎ ነበር እኮ…እሱን አወፍር ብዬ ያረድኩት ሙክት አንድ በረት ይሞላል…” (ይሳሳቃሉ)
    ዙሪያችሁ ያሉ ሰዎች ልክ በሪሞት ኮንትሮል ይመስል በአንድ ጊዜ ግንባራቸው መስመር ያለው ሉክ መስሎ ቁጭ!
    “ከውሀ በስተቀር ምንም ቀምሶ የማያውቅ” ሰው የምትባሉ ናችሁ እኮ! “ለምን አንድ ሁለት ቢራ አንጠጣም…” ለማለት እንኳን ‘እናስቀይመዋለን’ ተብሎ ተፈርቶ ከማኪያቶ ውጪ አትጋበዙም እኮ!
    በ‘መልካም ጠባያችሁ’ የተነሳ “ለምንድነው ዓለም አቀፍ ሽልማት የማይሰጠው…” ብለው የሚቆጩላችሁ ብዙ ነበሩ እኮ! ‘ዘመዶች’ ሊበቃቸው ነው!
    “እሱንማ ተዪው…ያቺን የእድር ዳኛውን ልጅ ያደረጋት ትዝ አይልሽም…አባቷ እስከ ዛሬ እኮ ቂም እንደያዙ ነው…”
    እናማ… እንግዳ ማስተናገድ አስቸጋሪ ነው። የምንጋብዘው እንኳን ‘ሬድ ሌብል’ ምናምን ሊኖረን ‘ሬድ’ መልክ ያላት ቲማቲምም የቅርብ ሩቅ ሆናብናለች፡፡
    ደህና ሰንብቱልኝማ!
    እንግዳ እና ‘ሬድ ሌብል’ ኤፍሬም እንዳለ እንዴት ሰነበታችሁሳ! ስሙኝማ…አንድ የምናውቀው ሰው እቤቱ የዘመድ እንግዶች ድንገት ይመጡበታል። እንዳጋጣሚ ሆኖ ከተገናኙ ረጅም ጊዜ ነበር። ቀድመው ሳይደውሉ ወይም በሌላ መንገድ እንዲያውቅ ሳያደርጉት አንድ እሁድ ቀን ‘ከች’ ይላሉ፡፡ እሱ ደግሞ ኑሮ ትንሽ ጠመም ብሎበት ከሚስቱ ጋር ጀርባ አዙረው መተኛት ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ ቂ…ቂ…ቂ…(በኑሮም ቅጣት፣ ‘በዛም’ ቅጣት!) ደግሞላችሁ…“ከሬድ ሌብል፣ ከኋይት ሆርስ፣ ከቆርቆሮ ቢራ የትኛው ይሻልሀል?” ብሎ ልግስና ቀርቷል። እናማ… ሚስቱ ወጣ ትልና ከእንትና ሱቅ በዱቤ ለስላሳ ምናምን ገዛዝታ ትመጣለች፡፡ ምን ቢሆን ጥሩ ነው…የእንግዶቹ ፊት ‘አሸቦ’ መሰለላችሁ። ውስኪውስ? ቆርቆሮ ቢራውስ! “ይሄ ጥሬ ሥጋ ሙልጭ ብሎ ካላለቀማ መጣላታችን ነው!” የሚባለው ያዙኝ፣ ልቀቁኝ ግብዣውስ! ‘እንግዶቹ’ በስንት ጊዜያቸው እግር ጥሏቸው ቢመጡ… የለመዱትን ውስኪና ጥሬ ሥጋ ስላላገኙ…እንዳኮረፉ ተቀምጠው፣ እንዳኮረፉ ሄዱና አረፉት፡፡ እኔ የምለው… ጊዜ እኮ ተለውጧል! ባለ ሸላይ መኪና እንደበዛው ሁሉ ባለጠማማ ጫማዎችም በዝተናል እኮ! በዕቃ ብዛት ‘ጧ’ ሊሉ የደረሱ የኮንዶሚንየም አንድ ክፍል ስቱዲዮ የሚያካክሉ ‘ፍሪጆች’ እንደበዙ ሁሉ፣ ሦስት ድስት አጣበው ሊይዙ የሚችሉ፣ አሁን ግን ነፋስ ሞልቶ የተረፋቸው ‘ፍሪጆች’ በዝተዋል እኮ! እናማ እንኳን ጥሬ ሥጋ ሊያቀርብ ሚስቱ የባልነት መብቱ ላይ እንኳን ማዕቀብ ጥላበት ይታዘንለታል እንጂ ይኮረፋል! ቂ…ቂ…ቂ… ስሙኝማ...እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ… የምር ግን ዘንድሮ ‘እንግዳ ማስተናገድ’ አስቸጋሪ እየሆነ ነው፡፡ በገንዘብ ችግር የጤፍ ፍጆታውን ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሀምሳ በመቶ የቀነሰው ሰውዬ እንዴት ነው ብላክ ሌብል ውስኪ፡ ዊንተር ምናምን ቮድካ ሊያቀርብልን የምንጠብቀው! ዘንድሮ አሥራ ምናምን ብር የገባች ስኒ ሻይም ከቀረበ ትልቅ ነገር ነው፡፡ ደግሞላችሁ…በፊት ከዘመድ ወይም ከጓደኛ ‘እንግዳ’ ጋር እንደ ልባችን እናወራ ነበር፡፡ አለ አይደል … “ምን ይለኛል?” “ደግሞ ቀድታኝ ሄዳ ለማን እንደምትናገር ማን ያውቃል!” “እንዲህ አለች ብላ ከሰው ብታቆራርጠኝስ!” “‘እናንተን አይወዳችሁም ብሎ ቢያስጠቁረኝስ!” (ቂ…ቂ…ቂ… ልጄ ዘንድሮ ‘መጥላት’ ብቻ ሳይሆን ‘አለመውደድም’… ‘ጥርስ የሚያስነክስበት’ ዘመን ሆኗል።) አይነት ስጋቶች የሉብንም ነበር፡፡ መቀለድ ብንፈልግም ለሳቅ ያልነው ዞሮ እኛ የምንሳቀቅበት ይሆናል የሚል ስጋት አልነበረንም፡፡ ዘንድሮ ሁሉም ተለውጧል፡፡ እና በፊት ‘የኩሼ’ ቤት ወሬ እንኳ ሳንደባበቅ እናወራው የነበረውን ሰው “ከእንትን ፋብሪካ የገዛሁት አንሶላ እንደተመቸኝ ነገር…” ብንለው… የሆነ ‘ቡድን ውስጥ ልንከተት’ እንችላላን፡፡ (ሰው በሚጠጣው ቢራ ‘የእንትን ቡድን አባል’ የሚባልበት ዘመን! “ስንት ባንክ እያለ አንተ እዛ ባንክ ምን ወሰደህ!” የሚባልበት ዘመን!) ደግሞላችሁ…የሆነ ‘የዘመድ እንግዳ’ ይመጣል፡፡ እንዴት ናችሁ ምናምን አይነት ልውውጥ ይካሄዳል። “ባለቤትህ ደህና ነች?” “ደህና ነች፡፡” “ምነው፣ የለችም እንዴ?“ “አክስቷ ታመው ወደ አስኮ አካባቢ ሄዳለች…” ትላላችሁ፡፡ ዘመዶች ለጥቂት ጊዜ ዝም ይላሉ፡፡ ከዛም… “አክስቷ ሞታለች አልተባለም እንዴ?” “ይቺኛዋ በአባት በኩል ያለችው ነች፡፡” “ነ…ው!” የድምጹ ቃና “ድንቄም አክስት!” አይነት ነው፡፡ “ዘንድሮ አክስቴ አጎቴ እያሉ የሚሄዱ ሚስቶች ምንም ደስ አይሉኝም” ይባላል፡፡ እኔ የምለው…በአክስትና ለቅሶ ቤት ለሰልስት በማደር ማሳበብ ቀርቷል እኮ! ዘንድሮ ‘ሌላ ነገር ቢያስቡ’ እንኳን ምን ሰበብ ያስፈልጋል፡፡ “ጉዳይ አለኝ፣ ማታ ትንሽ እቆያለሁ…” ማለት በቂ ነው። እናማ… በሰላም የተቀመጠውን ሰው ‘የዘመድ እንግዶች’ ሚስቱን እንዲጠረጥር ሊያደርጉት ይሞክራሉ፡፡ ከሆኑ ሰዎች ጋር ሰብስብ ብላችሁ ባላችሁበት የድሮ ትምህርት ቤት ጓደኛ ይመጣል፡፡ “አጅሬው፤ አንተ እኮ ድሮም ቢሆን የዋዛ አልነበርክም፣፡” ስሙኝማ...አንዳንዴ የድሮ ጓደኛ ችግሩ ምን መሰላችሁ…ጨዋታ ያሳመረ ይመስለውና…በቃ፣ ኤድዋርድ ስኖውደን ሆኖ ቁጭ! ስንት ዘመን ሁሉ ከአገር ምስጢርነት ባልተናነሰ ስትጠብቁት የኖራችሁትን ሁሉ…አለ አይደል…አውላላ ሜዳ ላይ ያሰጣዋል ነው የምላችሁ። “ስማ..ያኔ ዘጠነኛ ክፍል ሳለን…ትዝ ይልሀል…አስረኛ ዲ ክፍል ጓሮ…” ብሎ ‘መቀባጠር’ ሲጀምር…ፈጠን ብላችሁ “አዎ… ጊዜ ይሮጣል አይደል!” ምናምን ትላላችሁ። ከዛም… “አንተ ግን የት ጠፍተህ ነው የከረምከው! ከተገናኘን ቆየን እኮ…” ድንበር ዙሪያ ግንብ መገንባት በሉት፡፡ ዝም ብሎ ከለፈለፈ ሁሉም ነገር በማግስቱ ጠዋት መብራት ባለበትም፣ መብራት በጠፋበትም (‘አብዛኛውን ቦታ’ ለማለት ያህል!) ሁሉ ይዛመትላችኋል። እሱዬው ግን የተቦተረፈ የጤፍ ጆንያ ምናምን ነገር ይሆንላችኋል፡፡ “ስማ እሷ ልጅ አለች እንዴ…” ሰውዬው አሞታል እንዴ! “እኔ እንጃ፣ የስንት ዘመን ወሬ ነው የምታወራው…” ስንት ነገር ተቀይሯል፡፡ ጭቃ ሹሞች ተለውጠዋል፣ ሚሌኒየሙ ተለውጧል፣ የእንትናዬዎች የዳሌ ቅርጽ ተለውጧል! እሱ የድሮ አስረኛ ዲ ክፍል ጓሮ ወሬ ያወራል! ይሄኔ የሆነ ሰው የኮረኮረው ይመስል ከት ብሎ ይስቃል፡፡ “ስማ…እኔ እኮ እስካሁን የማልረሳው ከንፈሯ እንደዛ የተፈነከተ ሀብ፣ ሀብ የመሰለው እንዴት አድርገህ ብትስማት ነው!…ቦይ ፍሬንዷ ሰምቶ ብረት ቦክስ ይዞ የመጣው ትዝ አይልህም!” ይሄኔ በቃ ኩላሊት፣ ጉበት ምናምን ቦታ ሲለዋወጡ ይታወቃችኋል፡፡ እንደ ምሳሌ የምትታዩትን ሰው! “ምን አይነት የተባረከ ቤተሰብ ውስጥ ነው ያደገው…” የምትባሉትን ሰው! “ሰው ቀና ብሎ አያይም፣ እንዴት አይነት የተባረከ ሰው መሰላችሁ!” የምትባሉትን ሰው! “ቁመቱ ባያጥር ኖሮ (ቂ…ቂ…ቂ…) ልጄን ከአራት ልጆቿ አባት አፋትቼ እድርለት ነበር…” የምትባሉትን ሰው! ደግሞላችሁ የዘመድ እንግዶች አሉላችሁ፡፡ የሆኑ የሥራ ባልደረባችሁ፣ ወይም የኮንዶሚኒየም ጎረቤት፡ (ይቅርታ…ከጎን ያለ በሩ ሁልጊዜ የሚዘጋ ቤት እንጂ ለካስ የኮንዶሚኒየም ጎረቤት የለም…) ብቻ የሆኑ ሰዎች አብረዋችሁ አሉ፡፡ እና አንዷ ‘ዘመድ’… “አንተ በቃ እምቢ አልክ አይደል…” ትላለች፡፡ የምን ነገር! በቃ… ‘ፈንጂ ወረዳው’ ፊታችሁ መጥቶ ድቅን፡፡ በኮንዶሚኒየሙ ‘ከጎናችሁ ወደሚኖረው’ ሰው ዘወር ብላችሁ… “የውሀውን ጉልበት ለምንድነው የማይጨመሩልን! እኔ’ጋ እኮ ብታያት እንደ ዓይን ጠብታ ነው የምትወርደው።” ‘ዘመድ’ ትቀጠላለች፡፡ ‘ምልክቱ’ አልገባትማ! “ያቺን የመሰለች ልጅ አግባ ስትባል እምቢ ብለህ አሁን ብታያት እንዴት አይነት ሴት ወይዘሮ መስላለች…ስንትከረፈፍ አመለጠችህ…” ሌላኛዋ ‘ዘመድ’ ትቀጥላለች… “እሱ እባክሽ ሲነግሩት መች ይሰማል..ድሮስ እንዴት ያስቸግረን እንደነበር አታስታውሺም!...” (ይሳሰቃሉ) የመጀመሪያዋ ትቀጥላላች… “እሱንማ ተዪው… ጎጃም በረንዳ እየሄደ አረቄውን ላይ በላይ መገልበጥ ለምዶ መለኪያዋን አክሎ ነበር እኮ…እሱን አወፍር ብዬ ያረድኩት ሙክት አንድ በረት ይሞላል…” (ይሳሳቃሉ) ዙሪያችሁ ያሉ ሰዎች ልክ በሪሞት ኮንትሮል ይመስል በአንድ ጊዜ ግንባራቸው መስመር ያለው ሉክ መስሎ ቁጭ! “ከውሀ በስተቀር ምንም ቀምሶ የማያውቅ” ሰው የምትባሉ ናችሁ እኮ! “ለምን አንድ ሁለት ቢራ አንጠጣም…” ለማለት እንኳን ‘እናስቀይመዋለን’ ተብሎ ተፈርቶ ከማኪያቶ ውጪ አትጋበዙም እኮ! በ‘መልካም ጠባያችሁ’ የተነሳ “ለምንድነው ዓለም አቀፍ ሽልማት የማይሰጠው…” ብለው የሚቆጩላችሁ ብዙ ነበሩ እኮ! ‘ዘመዶች’ ሊበቃቸው ነው! “እሱንማ ተዪው…ያቺን የእድር ዳኛውን ልጅ ያደረጋት ትዝ አይልሽም…አባቷ እስከ ዛሬ እኮ ቂም እንደያዙ ነው…” እናማ… እንግዳ ማስተናገድ አስቸጋሪ ነው። የምንጋብዘው እንኳን ‘ሬድ ሌብል’ ምናምን ሊኖረን ‘ሬድ’ መልክ ያላት ቲማቲምም የቅርብ ሩቅ ሆናብናለች፡፡ ደህና ሰንብቱልኝማ!
    0 Comments 0 Shares
  • ጀንበሮቹ
    አጭር ልብወለድ
    በአለማየሁ ጌትነት (ኢብታ)
    በአንድ ዘመን በሩቅና ሩቅ ቦታ …. ሁለት ጨቅላዎች …….. ከየአባታቸው ወገብ ተስፈንጥረው …… ከእናታቸው ስጋ … ስጋ ነስተው …… የአብ እስትንፋስን ወርሰው …….ወዲህ መጡ - ወደ እናት ሀገር ጦቢያ፡፡
    …….ሞሳዎቹ አፈሩን ፈጩ፣ ውሃዋን ተራጩ፤ ጥርሷን ነክሳ ከሌላት ሞጣ /አጣ ሳይሆን ያንች አይሆንም ተብላ/ … እልፍ አልፋ ጠብ ከምታደርገው የእውቀት መና ….እነሆ መናውን ቆጥባችሁ ብቻ ሳይሆን አባዝታችሁ ተጠቀሙበት አለች፡፡ ...... እነሱቴ! ይልቅ በገለጠችላቸው አይን ነውርሽን አየን አሉ፡፡ …….ዳርሽ አልሰለጠነም ሲሉም ተቹ። ......እዚያ እሷ …እዚህ እሷ ብትሆንም፣ አንዱ ከአንዱ፣ ሌላኛውም ከሌላኛው ጥግ ወደ አማካኞች ፈረጠጡ። እናት ናትና ተቀበለች፤ ቀረን ያሉትን ርዝቅም ባንድ መዓድ አቋደሰች፡፡
    ….በአይኖ ስርም እንደ ተወዳጅ ያድጉ ነበር …በአይኖ ስርም ክፉም ደግም ያደርጉ ነበር …….ባይኖ ስርም ሳሉ፤ “ብላቴናዎችሽ ጎበዞች ሆነዋልና መንጋሽን ይጠብቁ፤ በመንጋዎችሽ ላይም በቅን ልቦና ይፍረዱ፤ ዳኝነትም ይቀመጡላቸው” አሏት፡፡
    እርሷም፤
    “ቀበሮ ከበግ ግልገል ከተጫወተ ወይ ቁንጣን እስኪያስጨንቀው በልቷል …አልያም የበግ ግልገል እንዲበላ አልተገለጠለትም …ልቦናውም ዋዥቷል። ……አይኑ የተከፈተ ጊዜ ግን ወዮ! ለግልገል ……ወዮላት ለናቷ” አለቻቸው
    እነሱ ግን፤
    “እናታለም፤ አየሽ የእርጅናሽን ስር መስደድ …አየሽ የሁሉ ነገርሽን መጃጀት ……እኛ ያልን ሌላ አንች ‘ምጠቅሽ ሌላ፡፡ …እናታለም ካንቺ የወረሱትን ድንቁርና እንግፈፍ …..ላያቸው ላይ ያጀፈጀፈውን ወግ አጥባቂነት እንሸልት …..ከነሱ ወጥተናል ….የራስ ጸጉራቸውን ቆጥረናልና ….መሻታቸውን እናውቃለን። ‘ሚፈልጉትንም አያውቁምና ‘ሚያስፈልጋቸውን ‘ንስጣቸው፡፡ ...የልዩነት አጋራቸውም ይራገፍ” …እና ሌላ ብዙ አሏት፤ አብዝተውም “መንጋውን ከኛ በላይ ያወቀው ላሳር”….ሲሉ እስክትደነቁር ነገርዋት። ..የመሰሎቻቸውም ቁጥር እንገሯን ጠብቶ በርክቷልና በፊቷ እንደ ባህር አሸዋ ፈሰሱ……ባንድነትም፤ “ኋላ ቀርነት ኋላ ይቅር! …ኢትዮጵያ ትቅደም! ….የዘመን ልጆች ገበሬ ወይፈኑን ባለሙያ ይሆን ዘንድ እንዲቆረቁብ …..መንጋዎቹን ቆርቁበን በለምለሙ እናውላለን!!” አሏት እርሷም፤
    “ፍየል ተራራው ትቦርቅበት ዘንድ ምቹዋ ነው!…የቁጥቋጦው እሾክም ያጠነክራታል …..ትቃርመው …ከሀሩርም ትከለልበት በቂዋ ነው፡፡ ….ዛዲያ ከመስኩ ምን አላት፤ …ለግመሎችስ የቀይ አፈር ሽታ ምናቸው ነው፡፡ ….ነጋ ጠባ ሽኮናቸውን ‘ሚያረሰርስ፣ ውሃስ ጥማትን ካጡ ምን ሊበጃቸው፤ …ልጆቸ ወፍ እንደ ሀገሯ ትዘምራለችና ዝማሬዋ ስላልጣማችሁ ብቻ አለቀሰች ትሏት አይገባም፡፡ …ከአፈር ‘ሚጋፋው ..ከአፈር ‘ሚላፋው ማረሻ ‘ንኳ ተፈጥሮበታልና ….አይሰለች አይደክመውም፤…..ላፈሩም እጅ አይሰጥም፡፡ ….በግብግቡም እንደ እባብ ቆዳውን እየሸለቀቀ ሲያበራ ይኖራል …..ያለ ተፈጥሮው ያስቀመጣችሁት……ያለ ግብሩ ያሳረፋችሁት ዕለት ግን…..ደረቱን የቀረደደው አፈር በተጋደመበት ሲሳብ ይመጣል ….እንደ አልባሌም ከጥቅም ውጭ ያደርገዋል፡፡ መንጎችም በመቀርደድ ‘ሚበረቱ ማረሻና…. በመቀርደድ ‘ሚፋፉ አፈር ናቸውና፤ ለይታችሁ አታውቋቸውም፡፡ …..ከነሱ ብትወጡም እነሱን አደላችሁም …ናቸው ያሏችሁን አንጠለጠላችሁ ‘ንጅ፣ አንዳች እንኳ አላስተዋላችሁም …..በደፈናው ትወጡባቸው፣ እንደ ዘንዶም ትውጧቸው ዘንድ አሰፍስፋችኋል” ….ስትል ሙግቷን አቀረበች፡፡
    ግና በጀ አላሉም፤ እልፍና እልፍ እየሆኑ ሄደው ነበርና በምድሪቱ ስልጣኔን አፈሰሱ፤ ስርአትንም ዘረጉ። …..ሁለቱ ማቲዎችም በመንጎቹ ላይ ሊፈርዱ በሸንጎ ተቀማጭ ሆኑ፡፡
    …አንዱም በልቡ ያመነውን እንደዛው እያደረገ …..ወገቡ እስኪጎብጥ፣ አይኑም እስኪደክም መንጋዎችን ቆረቆበላት፡፡
    ….ሌላውም ልቡ የወደደውን እንደዛው እያደረገ …. ጨጓራው እስኪገጠብ ….. ደሙም እየጎሸ እስኪያብጠው ተጋ፡፡
    * * *
    የጮራነት እድሜያቸው ባከተመ፣ ቀትርነታቸውም ባለፈ ጊዜ ….ጀንበሮቹ ሳይጠልቁ እናታቸውን ይገናኙ ዘንድ ወደዋልና ወደ እሷ መጡ።
    እንደ ልቡ ያደረገው ቀጭን ሰውም ስለሱ፤
    “በርግጥ ዋርካው የፍቅር ዋርካ ነው …. ቢሆንም ዘመኑን የጨረሰው በቃጠሎ ነውና ግንድ እንጂ ቅርንጫፍም ሆነ ቅጠል የለውም፤ ከብርድም ይከላከል ዘንድ አይቻለውም … ምድሪቱም ባጋተች ጊዜ ውሃ ለራሱ አልደበቀምና መልሶ ያገግም አይቻለውም ….ሊያምኑት ‘ንጅ ሊታመኑበት አይቻልም …አውሎ ንፋስም በመጣ ጊዜ በፊቱ ቅጥር አልተበጀምና አቅሙን ሰልሎ መነቀል እስኪቃጣው ይነቀንቀዋል …. በዙሪያው እጉም ብለው በተኮለኮሉትም ይበረታል …እንደ ርጉምም ይቀጠቀጣሉ ...ዛፉም ከማዘን የዘለለ ፋይዳ አያመጣም” ተብሏልና በደሉ ጉሮሮውን ተናንቆት ….ምላሱ ጋር ተከማችቶልና አፉን ከፈተ….
    “እናታለም….. ሌሎች ጸደይ ይኖሩ ዘንድ የተኖረን በጋ መንጎችሽ ስለምን እንደ ጥፋት ይመዛሉ ….ዋርካው እያንዳንዱን ቅጠል ለሌሎች ምቾት…እያንዳንዱንም ዝንጣፊ ለሌሎች ደህንነት … .በፍቅር መሰዋቱስ ስለ ምን ግድ አይሰጣቸውም፡፡ ….ማንም ከድርሻው ካልዘለለ ተቀማጭ እንዳይኖረው…ከፋንታ ማለፍም …ለራስ ጥፍር የሌላ ሳንባ መቀርጠፍ መሆኑስ ስለ ምን አይከሰትላቸውም” አላት እናቱም መለሰች፤
    “አንተ በኔም በመንጎቼም የተወደድክ ሆይ፤ አንተ መንጎችን ወደ ለምለሙ በሀቅ የነዳህ!…. በበርሃ ጥማት ስትቃጠል ካስገኘሀቸው ውሃ በፍኝህ ያልነካህ ሆይ… በ’ውኑ በመንጎች እንዳንተ የተወደደ.. እሚታመን አለን? …መንጎችስ ካንተ ውጭ አርጩሜ እንደያዘ ጠባቂ ሳይሆን ከመቀመጫው ሰፋ ብሎ ጉርብጥብጥ በማውጣቱ የሞተ ጸጉራቸውን ለማራገፍ እንደሚመቻቸው የሾላ ዛፍ የሚተሻሹት ይኖር ይሆን? …….ካንተ ሌላስ የእጁን ወደ አፋቸው እንጂ ያፋቸውን ወደ እጁ እንዳያደርግ አውቀው መጎምዠት ወደ ፊታቸው ከቶ እማይመጣ መንጎች ያሉት ይኖር ይሆን?
    “….ዛዲያ በመረጥከው መንገድ ከመፈቀርና ከመታመን ያለፈ …ፍስሀህን እሚያነሳሳ …ተድላህን ‘ሚጠራ ምን ይኖርና ነው …ፊትህ መከስከሱ …ምላስህ ክፉ ታወራ ዘንድ ከአፎቷ መውጣቷ” አለችው …..እርሱም፤ ”እናታለም አሁንም በድሮ በሬ ታርሳለችና …ከሷ ማውጋቱ ጉንጭ ማልፋት ነው …….ልትረዳም አትችልም” ሲል ተከዘ፡፡
    የልቡን መሻት የፈጸመው ወፍራም ሰውም ተራው ሆኗልና፤
    “እናታለም” አላት
    “እነሆ!... አለሁ የምወድህ ልጄ” ባለችው ጊዜም
    በመንጋው ተከቦ ብቸኝነት ተጫውቶበታል ….ጭፍራ አስከትሎ ፍርሀት ልቡን ደፍሮታል ….በሃይል ተሞልቶ አለመቻል አላግጦበታልና …ማይስቁ ግን ያገጠጡ ጥርሶች፣ ሁሌም ከሁሉም አሰልችተውት ……በፍርሃት እሚሸሹ አይኖች ….እሚንቀጠቀጡ እጆች ታክተውታልና …እፍኝ ጥሬ ለመደበቅ ዳሽንን ያክል የችግር የመከራ ተራራ ሲገነባ መስማት አማሮታልና ….. መበደሉ አንገሽግሾት እንዲህ አላት፤
    “እናታለም፤ እውን እንቦሳው ይጠባ ዘንድ ጥገቷ መመገቧ ሀጢያት ነው ….ያትክልት ቦታው ይጠበቅ ዘንድስ ቅጥሩን በተረፈ ምርቱ ማጠር ነውር ነው ….የበጎች መንጋስ በሰላም ያሸልብ ዘንድ ተኩላዎችን ማሳደድ ወንጀል ነው፡፡ …ከነብር የታደጓት ፍየልስ እንባ ታክል ወተት ብትለግስ ነፍስዋ ከስጋዋ ትለያለች? ….በቁጥቋጦ ገብቶ መውጫ በማጣቱ ያላዝን የነበረ ግመልስ፣ ነጻ አውጥተው ቢቀመጡት ሻኛው ይቀልጣል፡፡ ….ከእረኛ ውሾች መሀል እያበራገገ ግጦሹን ያስተጓጎለውን መገሰጽ ክፋት ነው …. እንደ ልዩ ፍጥረት ያስቆጥራል፤ ……..ጨካኝ እኩይስ ያስብላል”
    ምላሱም ከመናገር በተገታች፣ አንደበቱም በቀዘቀዘ ጊዜ እናቱ በእርጋታ መለሰች ..አለችም፤
    “የምወድህ ልጀ!.... በኔም በመንጎችም ሃይልህ የታመነ ሆይ! …..አንተ ጠማማውን አቅኝ ….አለቱን በርቃሽ ….ሆይ! …በውኑ እንደ አንተ በመንጎቹ ‘ሚከበር ይኖር ይሆን …..እንደ አንተስ ቃሉ ‘ሚሰማ ….ትዕዛዙ ‘ማይሻር ከቀደሙት ተነስቶ ይሆን ….እንደ አንተስ ‘ሚታመኑበት …የታመኑበትንስ ‘ማይጥል ……ያንበሳ ደቦልን በግራ እጁ ‘ሚሰብር …..በቀጠረው ቅጥር ወጀብ ‘ሚመክት …..በተሸበረ ከተማ የድህነት ደሴት ‘ሚያበጅ በውኑ ይኖር ይሆን፡፡
    …..ዛድያ በመረጥከው መንገድ ከሀይልና መታመኛ ከመሆን የዘለለ ምን የከንፈርህን ጥግ ሊያላቅቅ ይችልና ነው ...ሳቅህ እንደ ሰማይ የራቀው፣ ፈገግታህ የጨነገፈው” አለችው፡፡
    እርሱም…. እንደቀደመው ልትረዳ አትችልም ሲል በልቡ ተከዘ፡፡
    (ተፈጠመ)
    * * *
    ጀንበሮቹ ከትካዜያቸው በተመለሱ ጊዜም ድምጻቸውን ዘለግ አድርገው እንዲህና እንዲያ በማለት ወደ መነሻቸው ተጓዙ …..ጀንበሮቹ ጠለቁ፡፡
    © ማድረግ ያለበትን በማድረግ የሚስቱን አፍ ዘግቶ፣ የልጆቹን ከርስ ሞልቶ፣ በምቹ አልጋው ‘ሚያንኮራፋ አባወራ የተባረከ ይሁን። …..በፈንታው ከጓደኞችህ አንሰህ አሳነስከን በሚል ሰበብ የሚገላመጥ ….በነካሽኝ ሰበብ በሚስቱ ‘ርግጫ ከ’ንቅልፉ ‘ሚናጠብ ባል የተረገመ ይሁን።
    © በምቹ ምኝታው እንቅልፍ የተኮረፈው …በቀን ‘ሚቃዥ …ከመንጋው ጥቃትን ‘ሚሰጋ እረኛ የተረገመ ይሁን፡፡ ……በፈንታው በመንጏቹ መሀል ንጹህ ህሊናውን ትራስ አድርጎ ‘ሚያንቀላፋ እረኛ የተባረከ ይሁን፡፡
    © መንጎቹ በሃይሉ ‘ሚታበዩበት፣ ስለ ሃይሉም ‘ሚከበር እረኛ የተባረከ ይሁን። …..በፈንታውም በምሳሌነት እሚጠቀስ፣ ምሳሌነቱን ሊከተሉት ‘ማይሹት እረኛ የተረገመ ይሁን፡፡
    © መንጎቹ በፍቅሩ የተነደፉለት፣ ስለ ፍቅሩም ‘ሚከበር እረኛ የተባረከ ይሁን፡፡ ……በፈንታውም በፍርሀታቸው ውስጥ ትንሽ ፍቅርን ሽቶ ‘ሚቅበዘበዝ እረኛ የተረገመ ይሁን።
    © ሰናዩን ጎዳና ሲያመላክት ላንተ ምን እንደበጀ ‘ሚባል፣ በአጓጉል ቸርነቱና ደረቅ ሀቅ፣ ልጆቹን ከጓደኞቻቸው በታች ያደረገ አባት የተረመ ይሁን።
    © ቀናውን ጏዳና ይይዙ ዘንድ ሲመክር “‘ምን አንተ” እሚባል፣ ውርሱ እንደ ሀጢያት ‘ሚቆጠር፣ ስሙን ለመጥራት ‘ሚያፍሩበት አባት የተረገመ ይሁን፡፡
    © ……ህሊናውን ሳይነቅል፣ ጥርስ የነቀሉ ልጆችን ያመጣ አባት የተረገመ ይሁን፡፡
    © ባልጠግብ ባይነቱ ልጆቹን የጓደኞቻቸው መጠቋቆሚያ ያደረገ አባት የተረገመ ይሁን፡፡
    ጀንበሮቹ አጭር ልብወለድ በአለማየሁ ጌትነት (ኢብታ) በአንድ ዘመን በሩቅና ሩቅ ቦታ …. ሁለት ጨቅላዎች …….. ከየአባታቸው ወገብ ተስፈንጥረው …… ከእናታቸው ስጋ … ስጋ ነስተው …… የአብ እስትንፋስን ወርሰው …….ወዲህ መጡ - ወደ እናት ሀገር ጦቢያ፡፡ …….ሞሳዎቹ አፈሩን ፈጩ፣ ውሃዋን ተራጩ፤ ጥርሷን ነክሳ ከሌላት ሞጣ /አጣ ሳይሆን ያንች አይሆንም ተብላ/ … እልፍ አልፋ ጠብ ከምታደርገው የእውቀት መና ….እነሆ መናውን ቆጥባችሁ ብቻ ሳይሆን አባዝታችሁ ተጠቀሙበት አለች፡፡ ...... እነሱቴ! ይልቅ በገለጠችላቸው አይን ነውርሽን አየን አሉ፡፡ …….ዳርሽ አልሰለጠነም ሲሉም ተቹ። ......እዚያ እሷ …እዚህ እሷ ብትሆንም፣ አንዱ ከአንዱ፣ ሌላኛውም ከሌላኛው ጥግ ወደ አማካኞች ፈረጠጡ። እናት ናትና ተቀበለች፤ ቀረን ያሉትን ርዝቅም ባንድ መዓድ አቋደሰች፡፡ ….በአይኖ ስርም እንደ ተወዳጅ ያድጉ ነበር …በአይኖ ስርም ክፉም ደግም ያደርጉ ነበር …….ባይኖ ስርም ሳሉ፤ “ብላቴናዎችሽ ጎበዞች ሆነዋልና መንጋሽን ይጠብቁ፤ በመንጋዎችሽ ላይም በቅን ልቦና ይፍረዱ፤ ዳኝነትም ይቀመጡላቸው” አሏት፡፡ እርሷም፤ “ቀበሮ ከበግ ግልገል ከተጫወተ ወይ ቁንጣን እስኪያስጨንቀው በልቷል …አልያም የበግ ግልገል እንዲበላ አልተገለጠለትም …ልቦናውም ዋዥቷል። ……አይኑ የተከፈተ ጊዜ ግን ወዮ! ለግልገል ……ወዮላት ለናቷ” አለቻቸው እነሱ ግን፤ “እናታለም፤ አየሽ የእርጅናሽን ስር መስደድ …አየሽ የሁሉ ነገርሽን መጃጀት ……እኛ ያልን ሌላ አንች ‘ምጠቅሽ ሌላ፡፡ …እናታለም ካንቺ የወረሱትን ድንቁርና እንግፈፍ …..ላያቸው ላይ ያጀፈጀፈውን ወግ አጥባቂነት እንሸልት …..ከነሱ ወጥተናል ….የራስ ጸጉራቸውን ቆጥረናልና ….መሻታቸውን እናውቃለን። ‘ሚፈልጉትንም አያውቁምና ‘ሚያስፈልጋቸውን ‘ንስጣቸው፡፡ ...የልዩነት አጋራቸውም ይራገፍ” …እና ሌላ ብዙ አሏት፤ አብዝተውም “መንጋውን ከኛ በላይ ያወቀው ላሳር”….ሲሉ እስክትደነቁር ነገርዋት። ..የመሰሎቻቸውም ቁጥር እንገሯን ጠብቶ በርክቷልና በፊቷ እንደ ባህር አሸዋ ፈሰሱ……ባንድነትም፤ “ኋላ ቀርነት ኋላ ይቅር! …ኢትዮጵያ ትቅደም! ….የዘመን ልጆች ገበሬ ወይፈኑን ባለሙያ ይሆን ዘንድ እንዲቆረቁብ …..መንጋዎቹን ቆርቁበን በለምለሙ እናውላለን!!” አሏት እርሷም፤ “ፍየል ተራራው ትቦርቅበት ዘንድ ምቹዋ ነው!…የቁጥቋጦው እሾክም ያጠነክራታል …..ትቃርመው …ከሀሩርም ትከለልበት በቂዋ ነው፡፡ ….ዛዲያ ከመስኩ ምን አላት፤ …ለግመሎችስ የቀይ አፈር ሽታ ምናቸው ነው፡፡ ….ነጋ ጠባ ሽኮናቸውን ‘ሚያረሰርስ፣ ውሃስ ጥማትን ካጡ ምን ሊበጃቸው፤ …ልጆቸ ወፍ እንደ ሀገሯ ትዘምራለችና ዝማሬዋ ስላልጣማችሁ ብቻ አለቀሰች ትሏት አይገባም፡፡ …ከአፈር ‘ሚጋፋው ..ከአፈር ‘ሚላፋው ማረሻ ‘ንኳ ተፈጥሮበታልና ….አይሰለች አይደክመውም፤…..ላፈሩም እጅ አይሰጥም፡፡ ….በግብግቡም እንደ እባብ ቆዳውን እየሸለቀቀ ሲያበራ ይኖራል …..ያለ ተፈጥሮው ያስቀመጣችሁት……ያለ ግብሩ ያሳረፋችሁት ዕለት ግን…..ደረቱን የቀረደደው አፈር በተጋደመበት ሲሳብ ይመጣል ….እንደ አልባሌም ከጥቅም ውጭ ያደርገዋል፡፡ መንጎችም በመቀርደድ ‘ሚበረቱ ማረሻና…. በመቀርደድ ‘ሚፋፉ አፈር ናቸውና፤ ለይታችሁ አታውቋቸውም፡፡ …..ከነሱ ብትወጡም እነሱን አደላችሁም …ናቸው ያሏችሁን አንጠለጠላችሁ ‘ንጅ፣ አንዳች እንኳ አላስተዋላችሁም …..በደፈናው ትወጡባቸው፣ እንደ ዘንዶም ትውጧቸው ዘንድ አሰፍስፋችኋል” ….ስትል ሙግቷን አቀረበች፡፡ ግና በጀ አላሉም፤ እልፍና እልፍ እየሆኑ ሄደው ነበርና በምድሪቱ ስልጣኔን አፈሰሱ፤ ስርአትንም ዘረጉ። …..ሁለቱ ማቲዎችም በመንጎቹ ላይ ሊፈርዱ በሸንጎ ተቀማጭ ሆኑ፡፡ …አንዱም በልቡ ያመነውን እንደዛው እያደረገ …..ወገቡ እስኪጎብጥ፣ አይኑም እስኪደክም መንጋዎችን ቆረቆበላት፡፡ ….ሌላውም ልቡ የወደደውን እንደዛው እያደረገ …. ጨጓራው እስኪገጠብ ….. ደሙም እየጎሸ እስኪያብጠው ተጋ፡፡ * * * የጮራነት እድሜያቸው ባከተመ፣ ቀትርነታቸውም ባለፈ ጊዜ ….ጀንበሮቹ ሳይጠልቁ እናታቸውን ይገናኙ ዘንድ ወደዋልና ወደ እሷ መጡ። እንደ ልቡ ያደረገው ቀጭን ሰውም ስለሱ፤ “በርግጥ ዋርካው የፍቅር ዋርካ ነው …. ቢሆንም ዘመኑን የጨረሰው በቃጠሎ ነውና ግንድ እንጂ ቅርንጫፍም ሆነ ቅጠል የለውም፤ ከብርድም ይከላከል ዘንድ አይቻለውም … ምድሪቱም ባጋተች ጊዜ ውሃ ለራሱ አልደበቀምና መልሶ ያገግም አይቻለውም ….ሊያምኑት ‘ንጅ ሊታመኑበት አይቻልም …አውሎ ንፋስም በመጣ ጊዜ በፊቱ ቅጥር አልተበጀምና አቅሙን ሰልሎ መነቀል እስኪቃጣው ይነቀንቀዋል …. በዙሪያው እጉም ብለው በተኮለኮሉትም ይበረታል …እንደ ርጉምም ይቀጠቀጣሉ ...ዛፉም ከማዘን የዘለለ ፋይዳ አያመጣም” ተብሏልና በደሉ ጉሮሮውን ተናንቆት ….ምላሱ ጋር ተከማችቶልና አፉን ከፈተ…. “እናታለም….. ሌሎች ጸደይ ይኖሩ ዘንድ የተኖረን በጋ መንጎችሽ ስለምን እንደ ጥፋት ይመዛሉ ….ዋርካው እያንዳንዱን ቅጠል ለሌሎች ምቾት…እያንዳንዱንም ዝንጣፊ ለሌሎች ደህንነት … .በፍቅር መሰዋቱስ ስለ ምን ግድ አይሰጣቸውም፡፡ ….ማንም ከድርሻው ካልዘለለ ተቀማጭ እንዳይኖረው…ከፋንታ ማለፍም …ለራስ ጥፍር የሌላ ሳንባ መቀርጠፍ መሆኑስ ስለ ምን አይከሰትላቸውም” አላት እናቱም መለሰች፤ “አንተ በኔም በመንጎቼም የተወደድክ ሆይ፤ አንተ መንጎችን ወደ ለምለሙ በሀቅ የነዳህ!…. በበርሃ ጥማት ስትቃጠል ካስገኘሀቸው ውሃ በፍኝህ ያልነካህ ሆይ… በ’ውኑ በመንጎች እንዳንተ የተወደደ.. እሚታመን አለን? …መንጎችስ ካንተ ውጭ አርጩሜ እንደያዘ ጠባቂ ሳይሆን ከመቀመጫው ሰፋ ብሎ ጉርብጥብጥ በማውጣቱ የሞተ ጸጉራቸውን ለማራገፍ እንደሚመቻቸው የሾላ ዛፍ የሚተሻሹት ይኖር ይሆን? …….ካንተ ሌላስ የእጁን ወደ አፋቸው እንጂ ያፋቸውን ወደ እጁ እንዳያደርግ አውቀው መጎምዠት ወደ ፊታቸው ከቶ እማይመጣ መንጎች ያሉት ይኖር ይሆን? “….ዛዲያ በመረጥከው መንገድ ከመፈቀርና ከመታመን ያለፈ …ፍስሀህን እሚያነሳሳ …ተድላህን ‘ሚጠራ ምን ይኖርና ነው …ፊትህ መከስከሱ …ምላስህ ክፉ ታወራ ዘንድ ከአፎቷ መውጣቷ” አለችው …..እርሱም፤ ”እናታለም አሁንም በድሮ በሬ ታርሳለችና …ከሷ ማውጋቱ ጉንጭ ማልፋት ነው …….ልትረዳም አትችልም” ሲል ተከዘ፡፡ የልቡን መሻት የፈጸመው ወፍራም ሰውም ተራው ሆኗልና፤ “እናታለም” አላት “እነሆ!... አለሁ የምወድህ ልጄ” ባለችው ጊዜም በመንጋው ተከቦ ብቸኝነት ተጫውቶበታል ….ጭፍራ አስከትሎ ፍርሀት ልቡን ደፍሮታል ….በሃይል ተሞልቶ አለመቻል አላግጦበታልና …ማይስቁ ግን ያገጠጡ ጥርሶች፣ ሁሌም ከሁሉም አሰልችተውት ……በፍርሃት እሚሸሹ አይኖች ….እሚንቀጠቀጡ እጆች ታክተውታልና …እፍኝ ጥሬ ለመደበቅ ዳሽንን ያክል የችግር የመከራ ተራራ ሲገነባ መስማት አማሮታልና ….. መበደሉ አንገሽግሾት እንዲህ አላት፤ “እናታለም፤ እውን እንቦሳው ይጠባ ዘንድ ጥገቷ መመገቧ ሀጢያት ነው ….ያትክልት ቦታው ይጠበቅ ዘንድስ ቅጥሩን በተረፈ ምርቱ ማጠር ነውር ነው ….የበጎች መንጋስ በሰላም ያሸልብ ዘንድ ተኩላዎችን ማሳደድ ወንጀል ነው፡፡ …ከነብር የታደጓት ፍየልስ እንባ ታክል ወተት ብትለግስ ነፍስዋ ከስጋዋ ትለያለች? ….በቁጥቋጦ ገብቶ መውጫ በማጣቱ ያላዝን የነበረ ግመልስ፣ ነጻ አውጥተው ቢቀመጡት ሻኛው ይቀልጣል፡፡ ….ከእረኛ ውሾች መሀል እያበራገገ ግጦሹን ያስተጓጎለውን መገሰጽ ክፋት ነው …. እንደ ልዩ ፍጥረት ያስቆጥራል፤ ……..ጨካኝ እኩይስ ያስብላል” ምላሱም ከመናገር በተገታች፣ አንደበቱም በቀዘቀዘ ጊዜ እናቱ በእርጋታ መለሰች ..አለችም፤ “የምወድህ ልጀ!.... በኔም በመንጎችም ሃይልህ የታመነ ሆይ! …..አንተ ጠማማውን አቅኝ ….አለቱን በርቃሽ ….ሆይ! …በውኑ እንደ አንተ በመንጎቹ ‘ሚከበር ይኖር ይሆን …..እንደ አንተስ ቃሉ ‘ሚሰማ ….ትዕዛዙ ‘ማይሻር ከቀደሙት ተነስቶ ይሆን ….እንደ አንተስ ‘ሚታመኑበት …የታመኑበትንስ ‘ማይጥል ……ያንበሳ ደቦልን በግራ እጁ ‘ሚሰብር …..በቀጠረው ቅጥር ወጀብ ‘ሚመክት …..በተሸበረ ከተማ የድህነት ደሴት ‘ሚያበጅ በውኑ ይኖር ይሆን፡፡ …..ዛድያ በመረጥከው መንገድ ከሀይልና መታመኛ ከመሆን የዘለለ ምን የከንፈርህን ጥግ ሊያላቅቅ ይችልና ነው ...ሳቅህ እንደ ሰማይ የራቀው፣ ፈገግታህ የጨነገፈው” አለችው፡፡ እርሱም…. እንደቀደመው ልትረዳ አትችልም ሲል በልቡ ተከዘ፡፡ (ተፈጠመ) * * * ጀንበሮቹ ከትካዜያቸው በተመለሱ ጊዜም ድምጻቸውን ዘለግ አድርገው እንዲህና እንዲያ በማለት ወደ መነሻቸው ተጓዙ …..ጀንበሮቹ ጠለቁ፡፡ © ማድረግ ያለበትን በማድረግ የሚስቱን አፍ ዘግቶ፣ የልጆቹን ከርስ ሞልቶ፣ በምቹ አልጋው ‘ሚያንኮራፋ አባወራ የተባረከ ይሁን። …..በፈንታው ከጓደኞችህ አንሰህ አሳነስከን በሚል ሰበብ የሚገላመጥ ….በነካሽኝ ሰበብ በሚስቱ ‘ርግጫ ከ’ንቅልፉ ‘ሚናጠብ ባል የተረገመ ይሁን። © በምቹ ምኝታው እንቅልፍ የተኮረፈው …በቀን ‘ሚቃዥ …ከመንጋው ጥቃትን ‘ሚሰጋ እረኛ የተረገመ ይሁን፡፡ ……በፈንታው በመንጏቹ መሀል ንጹህ ህሊናውን ትራስ አድርጎ ‘ሚያንቀላፋ እረኛ የተባረከ ይሁን፡፡ © መንጎቹ በሃይሉ ‘ሚታበዩበት፣ ስለ ሃይሉም ‘ሚከበር እረኛ የተባረከ ይሁን። …..በፈንታውም በምሳሌነት እሚጠቀስ፣ ምሳሌነቱን ሊከተሉት ‘ማይሹት እረኛ የተረገመ ይሁን፡፡ © መንጎቹ በፍቅሩ የተነደፉለት፣ ስለ ፍቅሩም ‘ሚከበር እረኛ የተባረከ ይሁን፡፡ ……በፈንታውም በፍርሀታቸው ውስጥ ትንሽ ፍቅርን ሽቶ ‘ሚቅበዘበዝ እረኛ የተረገመ ይሁን። © ሰናዩን ጎዳና ሲያመላክት ላንተ ምን እንደበጀ ‘ሚባል፣ በአጓጉል ቸርነቱና ደረቅ ሀቅ፣ ልጆቹን ከጓደኞቻቸው በታች ያደረገ አባት የተረመ ይሁን። © ቀናውን ጏዳና ይይዙ ዘንድ ሲመክር “‘ምን አንተ” እሚባል፣ ውርሱ እንደ ሀጢያት ‘ሚቆጠር፣ ስሙን ለመጥራት ‘ሚያፍሩበት አባት የተረገመ ይሁን፡፡ © ……ህሊናውን ሳይነቅል፣ ጥርስ የነቀሉ ልጆችን ያመጣ አባት የተረገመ ይሁን፡፡ © ባልጠግብ ባይነቱ ልጆቹን የጓደኞቻቸው መጠቋቆሚያ ያደረገ አባት የተረገመ ይሁን፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • የአንጋፋው ሃያሲ አብደላ እዝራ ማስታወሻ ገጽ
    ከአዘጋጁ፡-
    አንጋፋው ሃያሲ አብደላ እዝራ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ከተለየን እንደዘበት አንድ ዓመት ሞላው፡፡ በዚህ አንድ ዓመት በእርግጥም ጥበብ ብዙ እንደጎደለባት በትክክል ተረድተናል - ተገንዝበናል፡፡ ይሄን ጊዜ የስንቱን ደራሲያንና ገጣሚያን የፈጠራ ሥራዎች ያስነብበን፣ ያስቃኘን ያስተነትነን እንደነበር ስናስብ ሀዘናችን ይበረታል፤ ቁጭታችም እንደዛው፡፡ ግን ምን ያደርጋል? እሱ አንዴ አርፏል፡፡ ግና ትንፋሹ እስክታቆም ድረስ ለጥበብና ለጠቢባን ዕድገትና መሻሻል ብዙ ለፍቷል- ከልቡ፡፡ አብደላ የጥበብ ጠበቃ ነበር፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጣ በዓይነትና በብዛት እንድታድግ፣ በሳምንት ሁለቴ እንድትወጣም ይመኝ ነበር፡፡ አዲስ አድማስን ይወዳት ነበር - ከልቡ፡፡ የአንደኛ ዓመት ሙት ዓመቱን ለመዘከርና ጥበባዊ ፍቅሩንና ትጋቱን እንዲሁም ውለታውን ለማስታወስ፣ የራሱን በህይወት ሳለ የወጣ አንድ የሂስ ፅሁፍና ደራሲ ደረጀ በላይነህ የከተበለትን “ጥበባዊ እንጉርጉሮ” ለአንባቢያን አቅርበናል፡፡ ገፁንም የአብደላ እዝራ
    ማስታወሻ አድርገነዋል፡፡ ፈጣሪ ነፍሱን በመንግስተ ሰማያት ያኑርለት፡፡
    “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ሂሳዊ ቅርበት
    ዕዝራ አብደላ
    ስለ አዳም ረታ ልቦለድ ውበትና ጥልቀት በመጠኑ ነው የተነካካው። ከደራሲው ጋር በተደረገ ውይይት እና በጥቂት የጥናት ወረቀቶች በአመዛኙ ስለ አጻጻፍ ይትበሃልና ዘዬ ነው የተተኮረው። “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ሰባት ትረካዎች ያስነብበናል፤ ስድስቱ ሆላንድ ሳለ ነው የተፈጠሩት። (1987 ) በገፅ መጠን “መች ትመጣለህ?” አጭር ልቦለድ ነው፤ የተቀሩት እንደ novella እምቅ ናቸው። ሰባቱም ብርቅ ትረካ ስለሆኑ፥ እያንዳንዱ የግሉን ኮስታራ ቆይታ ይማጠናል። ይህ ሂስ-ቀመስ ጽሑፍ፥ ሀምሳ ገፅ በፈጀ የስብስቡ ርዕስ በሆነው “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ላይ ብቻ ያተኩራል። ከዚህ ልቦለድ የተወሰኑ ገጾች ተመርጠው የዘመኑን መንፈስ -zeitgeist- በተለይ በገፀባህሪይዋ ምስራቅ ህይወትና እንግልት ላይ ባሳደረው የልቡና ወረራ ላይ ያጠነጠነ የአብረሃም ገዛኸኝ ፊልም ተሰርቷል። “ሃሜት፥ ጥላቻ፥ ውሸትና ቅናት የሞራል ወንጀሎች ... ከግለሰብ አልፈው ... ሀገር የማፍረስ አቅማቸው” በፊልሙ ተስተውሏል። ትረካው ግን የዘመን መንፈስ ክስተቶች ውጤት አይደለም። የግለሰብ ማንነት አቅምና ረግረግነት፥ ብሎም የልጅነት ዳራ የጐልማሳን ዛሬነት ሲቧጥጥ፥ ሰው ለራሱም ለሌላውም ሰቆቃ ይሆናል። ለማኅበረሰቡ እምነት ግለሰብ ሲገዛ -እንደ ታደሰ- እንግልት የሸሸገ ሰላም እስከ መላበስ ድረስ ትረካው ይፍታታል። የዶክተር በድሉ ዋቅጅራ ልዩ አሻሚ መንቶ፤ ምስራቅ እና ሎሚ ሽታ ይነጠቁበታል። “እኔ ምኑን ተጐዳሁ፥ ላንቺ ይብላኝልሽ እንጂ / እንደ መንፈስ ውስጤ ሳኖርሽ፥ አካል ሆነሽ ስትሄጂ” እንደ ስዕል የመንፈስ ቢጋር ውስጥ መታጠር የመረጠችው ምስራቅ፥ መቃኑን ነቃቅላ አካል ሆና ነፃ ከወጣች ሎሚ ሽታ እኩል ተቀርፀዋል።
    ከጭብጦች አንዱ የሆነው የሰዋዊ ግንኙነት ረቂቅ ገፅታዎች፥ በተለይም የወንድ-የሴት ሰበቃ እስከ ውስጣዊ ሥነልቦናዊ ጓዳ የመጥለቅ ምትሃት፥ አዳም ረታ ተክኖበታል። የስምንት ሴቶች ልቦለድ (143 ገፅ የፈጀው) “ኩሳንኩስ” በተመስጦ ሲነበብ፣ የሀዲስ ዓለማየሁ ሰብለወንጌል፥ የበዐሉ ግርማ ሉሊት፥ ተሻግሮም የቶልስቶይ ገፀባህሪ አና ካራኒን ... ይደበዝዛሉ። ይህ “ይወስዳል መንገድ፥ ያመጣል መንገድ” መጽሐፍ ውስጥ ያደፈጠው “ኩሳንኩስ” ወደፊት በሂሳዊ ንባብ ባባብለውም እነ ሰናይት፥ እትዬ ወርቄ፥ ሣራ ... ከምናቤ አይሰክኑም፤ እየተንጓለሉ ሰርክ እበረግጋለሁ። ከሰው ለላቀ ገፀባህሪ መደንገጥ ምን ይደንቃል? ዋሲሁን በላይ በአርምሞ አግኝቶታል። “ትበረግጋለች ነፍሴ በትንሽ ኮሽታ / ሠቀቀን ገደላት ጊዜው ላይ ተኝታ” ዝነኛው ባለቅኔ Ezra Pound ስለ ግጥም አጻጻፍ የመሰከረው ለአዳም ረታ የቋንቋ ጥበብ ይመጥነዋል። “Great literature is simply language charged with meaning to the utmost possible degree.” የአብይ ሥነጽሑፍ አስኳል በትርጓሜ፥ በአንድምታ የተለበለበ ቋንቋ ነው እንደማለት። ጥቃቅን ግን ሌላው ግለሰብ ሊመሰጥበት ቀርቶ ልብ የማይለውን ምስል፥ እንቅስቃሴ ወይም የሆነ ድርጊት የአዳም ረታ ብዕር ሲፍቀው፥ ሲያሻሸው የሚፈልቅለት ውበት-አስቀያሚነት እስከ ፍፁም ንዝረት፥ እስከ አስደንጋጭ ግርምት ይረቃል፤ እሳቦትና ምናባችን ይታመሳሉ። ለአዲስ በኩር ክስተት አሁንም እንበረግጋለን። (በአስረጅ እመለስበታለሁ)። አዳም፥ በኑሮ ውጣ ውረድ ተጠምደው ሲያቃስቱ፥ ሲቦርቁ ገፀባህሪያት ቀረፀ እንጂ አንዱን እኩይ፥ ሌላውን በጐ በማለት አይፈርድም። አንባቢ ነው እንደ ብስለቱ፥ እንደ ገጠመኙ የባለታሪኮችን ህይወትና አቋም የሚመነዝረው። ለዚህም ነው ሎሚ ሽታ ለአንዱ አርአያ እንስት ስትሆን፥ ሌላው የሚያወግዛት። ደራሲው በገፀባህሪያት ድርጊት ሳይታቀብ ውስጠታቸውን ሲቦረቡር ገለጣው ስዕሉ ያስደምማል። አንድ መነኩሴ ለመምህሩ ያቀረበው ጥያቄ ይታወሰኛል። ስለ ስዕል የሚያትት መጽሐፍ ነው። “ብርሃን ማጤን፥ ጥላውን መሳል” ከሚል ምዕራፍ የተተረከ ነው።
    “እኔ ምንድነኝ?” ብሎ ጠየቀ መነኩሴው።
    መምህሩም መለሰ፤ “ከውስጥህ ያደባ ድብቅ ነገር አለ። ዘልቆህ የተሸሸገውን እንቅስቃሴ መላመድ አለብህ።”
    መነኩሴው እውስጡ ስለተሰወረው ነገር እንዲብራራለት ተማጠነ። መምህሩ በሃሳብ ከነጐደ በኋላ ዞር ብሎ መነኩሴውን አስተዋለና አይኑን ገለጥ፥ ጨፈን ብቻ አድርጐ ሄደ። ይህን ድርጊት - አይንን መጨፈንና መግለጥ- የመሰለ አፍታ መፈልፈል የሚችለው፥ ለፈጠራ ድርሰት የሚያበቃው አዳም ረታ ብቻ ነው። “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ን በማዟዛር የተለያየ ገጾቹን በጥቂት ክፍሎች ለማንበብ እሞክራለሁ።
    --- 1 ---
    መገለል
    ለስራ ወጥቶ ሲገባ ቀድሜው ከደረስኩ ጊዜው አያልፍልኝም ነበር። ኮቴውን ስሰማ እተቀመጥኩበት እደነግጥ ነበር። እቆምኩበት እደነግጥ ነበር። ዛሬ ድረስ የእርምጃው ዳና እንደ ሙዚቃ እንደ ከበሮ ቃና በጆሮዬ ውስጥ አለ። ከሶስት ከአራት ሰዎች መሃል የእግሩን አጣጣል መርጬ ማውጣት እችል ነበር። የሚያስቀና መልክ የሚያስቀና ቁመና ነበረው። በአልኮል እየፋቁ በሐሰት መረጃ እየተረተሩ እስኪያጠፉት ድረስ። ... ጠረኑ ልጄ ገና የተለቀመ ጥጥ ይመስል ነበር።
    (ምስራቅ ለልጇ ለታደሰ፥ ስለአባቱ ፍቅረስላሴ ካወጋችዉ የተቀነጨበ)
    [እቴሜቴ ሎሚሽታ ገፅ 105 ]
    ምስራቅ ልቧ ትርክክ ብሎ ለፍቅረሥላሴ የተርበተበተችው ገና በአፍላ እድሜዋ ነበር። “... ከኬክ ቤት(ብርቅ ነበር ያንጊዜ) እሱ ሲወጣ እኔ ልገባ ስል ... በሩ ጋ ሳየው፥ እዚህ ልቤን መታኝ፥ የማላመልጠው ነበር። ... ሌላ ሰው አስጠላኝ። ልቤ ግብት አለ። ያን ቀን ማታ ቤቴ ገብቼ ሙሉ ምሽት ሳስበው ነበር። አልጋዬ ላይ በጀርባዬ ተኝቼ ፈዝዣአለሁ፤ ዝም ብዬአለሁ።” ፍቅር አሸነፋት፤ ለባሌ ዳንስ ሃንጋሪ መሄድ ስትችል ቀረች። የህይወቷን አቅጣጫ የሚገራ ትምህርት፥ በመዳፏ ያለውን ተገን አሽቀንጥራ እንድትጥል የመውደድ ሃያልነት አስገደዳት፤ ከፍቅር ጉም በዳበሳ ተሰወረች። ከፍቅረሥላሴ ትዳር ይመስርታሉ። ፍቅሯን ሳታጣጥም ገና ነፍሰጡር ሳለች ባልየው በጓደኞቹ ወሬ ተደናቅፎ እየተገለላት፥ ስክሮ በውድቅት እቤት መመለስ ጀመረ። ፍቅረሥላሴ የረባ ስራ ነበረው። የተለያዩ ወንዶች ተኝተዋት እንደነበር አወሩለት፤ ልቡ ሻከረ። “ታድይ አባትህ ደም ስሩ ተግተርትሮ ሊፈነዳ ደርሶ ትልቅ ዕውነት ከሰማይ እንደ ወረደለት ሁሉ ... `አንዴ ጨዋ ነኝ ብለሽ የለ፥ ውሸትሽ ሲወጣ ለምን አትክጂ?` ይለኛል።” የቅድመ ትዳር ህይወቷን ነበር የሚያማው። የተወለደው ህፃን የሱን መልክ ስለወረሰ ለጥቂት ወራት ምስራቅ በፍቅር መፍካት ቻለች። ጥርጣሬው ግን አገርሽቶ ህፃኑ ታደሰ ገና ጡጦ ሳይጥል ፍቅረስላሴ ያርፋል። “አንድ ቀን ከገነት ሆቴል ወረድ ብሎ ቦይ ውስጥ ከቁሙ ወደቀና - ያየ ሲያወራ - የተሰበረ ቆሻሻ ጠርሙስ በአንገቱ ገባ። አለቀስኩ እንጂ ሲሞት። ... ሳንደሰት፥ እሱም በልጅነቱ እኔም ገና በልጅነቴ እንዲህ ምርር እንዳለን ሁሉ ነገር አለቀ።” ታደሰ የአባቱን ህልፈትና የጠባቸውን መነሻ ስለማያውቅ እናቱ በምትተርክለት ብቻ አስተሳሰቡ ይቦካል።
    ምስራቅ ለጥቂት ወራት አዝና ብድግ ብላ ቁዘማዋን ገፍፋ፥ አዲስ ሌላ ህይወት ለመጐንጐን አልባዘነችም። ተኮፍሳ ቀረች። በፍቅር የተሰበረ ልቧን መጠገን ተሳናት። የባሏን አሉባልተኛ ጓደኞች ጠልታ ራሷን አግልላ ማኅበረሰቡን ጭምር ተራገመች፤ አቄመች። ለነገዎቿ ከምታልም፥ ትናንቷን እየወለወለች ፈዘዘች። ታደሰን ለማሳደግ ግን በታይፒስትነት እየሰራች ዘለቀች። “ብትረባም ባትረባም ያንድ ገፅ ያልተበረዘች እሱን የማፍቀር ታሪኬን ይዤ አፈር እገባለሁ። ወደሥራዬ ስሄድና አስቤዛ ልገዛ ካልሆነ ለአስራ ሰባት አመታት ከቤት አልወጣሁም።” እንዴት ግለሰብ እንዲህ ሊሰበር ሊገለል ቻለ? የሰዓዳ መሀመድ አጭር ልቦለድ “የውድቅት ዕንባ” [ወንዞች እስኪሞሉ፥ 1998 ገፅ 109-127] ትዝ ይለኛል:: የሮቤል እናት ዩኒቨርስቲ የመግባት ነጥብ ብታመጣም ከድህነት ለመጠለል ትዳር ትመሰርታለች። ሆኖም የምታፍቅረው ባል ችላ ይላታል።
    የመጀመሪያ ባሌን እወደው ነበር። ግን አሁንስ እጠለዋለሁ? ታድያ የመጀመሪያ ልጄ አይኖቹ የሚረብሹኝ ለምን ይሆን?...
    የአንጋፋው ሃያሲ አብደላ እዝራ ማስታወሻ ገጽ ከአዘጋጁ፡- አንጋፋው ሃያሲ አብደላ እዝራ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ከተለየን እንደዘበት አንድ ዓመት ሞላው፡፡ በዚህ አንድ ዓመት በእርግጥም ጥበብ ብዙ እንደጎደለባት በትክክል ተረድተናል - ተገንዝበናል፡፡ ይሄን ጊዜ የስንቱን ደራሲያንና ገጣሚያን የፈጠራ ሥራዎች ያስነብበን፣ ያስቃኘን ያስተነትነን እንደነበር ስናስብ ሀዘናችን ይበረታል፤ ቁጭታችም እንደዛው፡፡ ግን ምን ያደርጋል? እሱ አንዴ አርፏል፡፡ ግና ትንፋሹ እስክታቆም ድረስ ለጥበብና ለጠቢባን ዕድገትና መሻሻል ብዙ ለፍቷል- ከልቡ፡፡ አብደላ የጥበብ ጠበቃ ነበር፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጣ በዓይነትና በብዛት እንድታድግ፣ በሳምንት ሁለቴ እንድትወጣም ይመኝ ነበር፡፡ አዲስ አድማስን ይወዳት ነበር - ከልቡ፡፡ የአንደኛ ዓመት ሙት ዓመቱን ለመዘከርና ጥበባዊ ፍቅሩንና ትጋቱን እንዲሁም ውለታውን ለማስታወስ፣ የራሱን በህይወት ሳለ የወጣ አንድ የሂስ ፅሁፍና ደራሲ ደረጀ በላይነህ የከተበለትን “ጥበባዊ እንጉርጉሮ” ለአንባቢያን አቅርበናል፡፡ ገፁንም የአብደላ እዝራ ማስታወሻ አድርገነዋል፡፡ ፈጣሪ ነፍሱን በመንግስተ ሰማያት ያኑርለት፡፡ “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ሂሳዊ ቅርበት ዕዝራ አብደላ ስለ አዳም ረታ ልቦለድ ውበትና ጥልቀት በመጠኑ ነው የተነካካው። ከደራሲው ጋር በተደረገ ውይይት እና በጥቂት የጥናት ወረቀቶች በአመዛኙ ስለ አጻጻፍ ይትበሃልና ዘዬ ነው የተተኮረው። “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ሰባት ትረካዎች ያስነብበናል፤ ስድስቱ ሆላንድ ሳለ ነው የተፈጠሩት። (1987 ) በገፅ መጠን “መች ትመጣለህ?” አጭር ልቦለድ ነው፤ የተቀሩት እንደ novella እምቅ ናቸው። ሰባቱም ብርቅ ትረካ ስለሆኑ፥ እያንዳንዱ የግሉን ኮስታራ ቆይታ ይማጠናል። ይህ ሂስ-ቀመስ ጽሑፍ፥ ሀምሳ ገፅ በፈጀ የስብስቡ ርዕስ በሆነው “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ላይ ብቻ ያተኩራል። ከዚህ ልቦለድ የተወሰኑ ገጾች ተመርጠው የዘመኑን መንፈስ -zeitgeist- በተለይ በገፀባህሪይዋ ምስራቅ ህይወትና እንግልት ላይ ባሳደረው የልቡና ወረራ ላይ ያጠነጠነ የአብረሃም ገዛኸኝ ፊልም ተሰርቷል። “ሃሜት፥ ጥላቻ፥ ውሸትና ቅናት የሞራል ወንጀሎች ... ከግለሰብ አልፈው ... ሀገር የማፍረስ አቅማቸው” በፊልሙ ተስተውሏል። ትረካው ግን የዘመን መንፈስ ክስተቶች ውጤት አይደለም። የግለሰብ ማንነት አቅምና ረግረግነት፥ ብሎም የልጅነት ዳራ የጐልማሳን ዛሬነት ሲቧጥጥ፥ ሰው ለራሱም ለሌላውም ሰቆቃ ይሆናል። ለማኅበረሰቡ እምነት ግለሰብ ሲገዛ -እንደ ታደሰ- እንግልት የሸሸገ ሰላም እስከ መላበስ ድረስ ትረካው ይፍታታል። የዶክተር በድሉ ዋቅጅራ ልዩ አሻሚ መንቶ፤ ምስራቅ እና ሎሚ ሽታ ይነጠቁበታል። “እኔ ምኑን ተጐዳሁ፥ ላንቺ ይብላኝልሽ እንጂ / እንደ መንፈስ ውስጤ ሳኖርሽ፥ አካል ሆነሽ ስትሄጂ” እንደ ስዕል የመንፈስ ቢጋር ውስጥ መታጠር የመረጠችው ምስራቅ፥ መቃኑን ነቃቅላ አካል ሆና ነፃ ከወጣች ሎሚ ሽታ እኩል ተቀርፀዋል። ከጭብጦች አንዱ የሆነው የሰዋዊ ግንኙነት ረቂቅ ገፅታዎች፥ በተለይም የወንድ-የሴት ሰበቃ እስከ ውስጣዊ ሥነልቦናዊ ጓዳ የመጥለቅ ምትሃት፥ አዳም ረታ ተክኖበታል። የስምንት ሴቶች ልቦለድ (143 ገፅ የፈጀው) “ኩሳንኩስ” በተመስጦ ሲነበብ፣ የሀዲስ ዓለማየሁ ሰብለወንጌል፥ የበዐሉ ግርማ ሉሊት፥ ተሻግሮም የቶልስቶይ ገፀባህሪ አና ካራኒን ... ይደበዝዛሉ። ይህ “ይወስዳል መንገድ፥ ያመጣል መንገድ” መጽሐፍ ውስጥ ያደፈጠው “ኩሳንኩስ” ወደፊት በሂሳዊ ንባብ ባባብለውም እነ ሰናይት፥ እትዬ ወርቄ፥ ሣራ ... ከምናቤ አይሰክኑም፤ እየተንጓለሉ ሰርክ እበረግጋለሁ። ከሰው ለላቀ ገፀባህሪ መደንገጥ ምን ይደንቃል? ዋሲሁን በላይ በአርምሞ አግኝቶታል። “ትበረግጋለች ነፍሴ በትንሽ ኮሽታ / ሠቀቀን ገደላት ጊዜው ላይ ተኝታ” ዝነኛው ባለቅኔ Ezra Pound ስለ ግጥም አጻጻፍ የመሰከረው ለአዳም ረታ የቋንቋ ጥበብ ይመጥነዋል። “Great literature is simply language charged with meaning to the utmost possible degree.” የአብይ ሥነጽሑፍ አስኳል በትርጓሜ፥ በአንድምታ የተለበለበ ቋንቋ ነው እንደማለት። ጥቃቅን ግን ሌላው ግለሰብ ሊመሰጥበት ቀርቶ ልብ የማይለውን ምስል፥ እንቅስቃሴ ወይም የሆነ ድርጊት የአዳም ረታ ብዕር ሲፍቀው፥ ሲያሻሸው የሚፈልቅለት ውበት-አስቀያሚነት እስከ ፍፁም ንዝረት፥ እስከ አስደንጋጭ ግርምት ይረቃል፤ እሳቦትና ምናባችን ይታመሳሉ። ለአዲስ በኩር ክስተት አሁንም እንበረግጋለን። (በአስረጅ እመለስበታለሁ)። አዳም፥ በኑሮ ውጣ ውረድ ተጠምደው ሲያቃስቱ፥ ሲቦርቁ ገፀባህሪያት ቀረፀ እንጂ አንዱን እኩይ፥ ሌላውን በጐ በማለት አይፈርድም። አንባቢ ነው እንደ ብስለቱ፥ እንደ ገጠመኙ የባለታሪኮችን ህይወትና አቋም የሚመነዝረው። ለዚህም ነው ሎሚ ሽታ ለአንዱ አርአያ እንስት ስትሆን፥ ሌላው የሚያወግዛት። ደራሲው በገፀባህሪያት ድርጊት ሳይታቀብ ውስጠታቸውን ሲቦረቡር ገለጣው ስዕሉ ያስደምማል። አንድ መነኩሴ ለመምህሩ ያቀረበው ጥያቄ ይታወሰኛል። ስለ ስዕል የሚያትት መጽሐፍ ነው። “ብርሃን ማጤን፥ ጥላውን መሳል” ከሚል ምዕራፍ የተተረከ ነው። “እኔ ምንድነኝ?” ብሎ ጠየቀ መነኩሴው። መምህሩም መለሰ፤ “ከውስጥህ ያደባ ድብቅ ነገር አለ። ዘልቆህ የተሸሸገውን እንቅስቃሴ መላመድ አለብህ።” መነኩሴው እውስጡ ስለተሰወረው ነገር እንዲብራራለት ተማጠነ። መምህሩ በሃሳብ ከነጐደ በኋላ ዞር ብሎ መነኩሴውን አስተዋለና አይኑን ገለጥ፥ ጨፈን ብቻ አድርጐ ሄደ። ይህን ድርጊት - አይንን መጨፈንና መግለጥ- የመሰለ አፍታ መፈልፈል የሚችለው፥ ለፈጠራ ድርሰት የሚያበቃው አዳም ረታ ብቻ ነው። “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ን በማዟዛር የተለያየ ገጾቹን በጥቂት ክፍሎች ለማንበብ እሞክራለሁ። --- 1 --- መገለል ለስራ ወጥቶ ሲገባ ቀድሜው ከደረስኩ ጊዜው አያልፍልኝም ነበር። ኮቴውን ስሰማ እተቀመጥኩበት እደነግጥ ነበር። እቆምኩበት እደነግጥ ነበር። ዛሬ ድረስ የእርምጃው ዳና እንደ ሙዚቃ እንደ ከበሮ ቃና በጆሮዬ ውስጥ አለ። ከሶስት ከአራት ሰዎች መሃል የእግሩን አጣጣል መርጬ ማውጣት እችል ነበር። የሚያስቀና መልክ የሚያስቀና ቁመና ነበረው። በአልኮል እየፋቁ በሐሰት መረጃ እየተረተሩ እስኪያጠፉት ድረስ። ... ጠረኑ ልጄ ገና የተለቀመ ጥጥ ይመስል ነበር። (ምስራቅ ለልጇ ለታደሰ፥ ስለአባቱ ፍቅረስላሴ ካወጋችዉ የተቀነጨበ) [እቴሜቴ ሎሚሽታ ገፅ 105 ] ምስራቅ ልቧ ትርክክ ብሎ ለፍቅረሥላሴ የተርበተበተችው ገና በአፍላ እድሜዋ ነበር። “... ከኬክ ቤት(ብርቅ ነበር ያንጊዜ) እሱ ሲወጣ እኔ ልገባ ስል ... በሩ ጋ ሳየው፥ እዚህ ልቤን መታኝ፥ የማላመልጠው ነበር። ... ሌላ ሰው አስጠላኝ። ልቤ ግብት አለ። ያን ቀን ማታ ቤቴ ገብቼ ሙሉ ምሽት ሳስበው ነበር። አልጋዬ ላይ በጀርባዬ ተኝቼ ፈዝዣአለሁ፤ ዝም ብዬአለሁ።” ፍቅር አሸነፋት፤ ለባሌ ዳንስ ሃንጋሪ መሄድ ስትችል ቀረች። የህይወቷን አቅጣጫ የሚገራ ትምህርት፥ በመዳፏ ያለውን ተገን አሽቀንጥራ እንድትጥል የመውደድ ሃያልነት አስገደዳት፤ ከፍቅር ጉም በዳበሳ ተሰወረች። ከፍቅረሥላሴ ትዳር ይመስርታሉ። ፍቅሯን ሳታጣጥም ገና ነፍሰጡር ሳለች ባልየው በጓደኞቹ ወሬ ተደናቅፎ እየተገለላት፥ ስክሮ በውድቅት እቤት መመለስ ጀመረ። ፍቅረሥላሴ የረባ ስራ ነበረው። የተለያዩ ወንዶች ተኝተዋት እንደነበር አወሩለት፤ ልቡ ሻከረ። “ታድይ አባትህ ደም ስሩ ተግተርትሮ ሊፈነዳ ደርሶ ትልቅ ዕውነት ከሰማይ እንደ ወረደለት ሁሉ ... `አንዴ ጨዋ ነኝ ብለሽ የለ፥ ውሸትሽ ሲወጣ ለምን አትክጂ?` ይለኛል።” የቅድመ ትዳር ህይወቷን ነበር የሚያማው። የተወለደው ህፃን የሱን መልክ ስለወረሰ ለጥቂት ወራት ምስራቅ በፍቅር መፍካት ቻለች። ጥርጣሬው ግን አገርሽቶ ህፃኑ ታደሰ ገና ጡጦ ሳይጥል ፍቅረስላሴ ያርፋል። “አንድ ቀን ከገነት ሆቴል ወረድ ብሎ ቦይ ውስጥ ከቁሙ ወደቀና - ያየ ሲያወራ - የተሰበረ ቆሻሻ ጠርሙስ በአንገቱ ገባ። አለቀስኩ እንጂ ሲሞት። ... ሳንደሰት፥ እሱም በልጅነቱ እኔም ገና በልጅነቴ እንዲህ ምርር እንዳለን ሁሉ ነገር አለቀ።” ታደሰ የአባቱን ህልፈትና የጠባቸውን መነሻ ስለማያውቅ እናቱ በምትተርክለት ብቻ አስተሳሰቡ ይቦካል። ምስራቅ ለጥቂት ወራት አዝና ብድግ ብላ ቁዘማዋን ገፍፋ፥ አዲስ ሌላ ህይወት ለመጐንጐን አልባዘነችም። ተኮፍሳ ቀረች። በፍቅር የተሰበረ ልቧን መጠገን ተሳናት። የባሏን አሉባልተኛ ጓደኞች ጠልታ ራሷን አግልላ ማኅበረሰቡን ጭምር ተራገመች፤ አቄመች። ለነገዎቿ ከምታልም፥ ትናንቷን እየወለወለች ፈዘዘች። ታደሰን ለማሳደግ ግን በታይፒስትነት እየሰራች ዘለቀች። “ብትረባም ባትረባም ያንድ ገፅ ያልተበረዘች እሱን የማፍቀር ታሪኬን ይዤ አፈር እገባለሁ። ወደሥራዬ ስሄድና አስቤዛ ልገዛ ካልሆነ ለአስራ ሰባት አመታት ከቤት አልወጣሁም።” እንዴት ግለሰብ እንዲህ ሊሰበር ሊገለል ቻለ? የሰዓዳ መሀመድ አጭር ልቦለድ “የውድቅት ዕንባ” [ወንዞች እስኪሞሉ፥ 1998 ገፅ 109-127] ትዝ ይለኛል:: የሮቤል እናት ዩኒቨርስቲ የመግባት ነጥብ ብታመጣም ከድህነት ለመጠለል ትዳር ትመሰርታለች። ሆኖም የምታፍቅረው ባል ችላ ይላታል። የመጀመሪያ ባሌን እወደው ነበር። ግን አሁንስ እጠለዋለሁ? ታድያ የመጀመሪያ ልጄ አይኖቹ የሚረብሹኝ ለምን ይሆን?...
    0 Comments 0 Shares
  • Piassa 1959
    Piassa 1959
    0 Comments 0 Shares
  • ስትሮክ እየጨረሰን ነው

    (መላኩ ብርሃኑ)
    ……………………………………

    ይህንን መረጃ ሳነብ ያገኘሁት ነው። ለሁላችንም እንዲጠቅም ወደአማርኛ መልሼዋለሁ። ስትሮክ የዕለት ከዕለት ችግራችን እየሆነና የሁላችንንም ጓዳ እያንኳኳ በመሆኑ መረጃው ይጠቅመናል ብዬ አስባለሁ። እባካችሁ ሼር በማድረግ እውቀት አሸጋግሩ። ምናልባት በዚህ መረጃ የአንድ ሰው ህይወት ታተርፉ ይሆናል።

    እኔ በበኩሌ ከ8 አመት በፊት ይህ መረጃ ቢኖረኝ ኖሮ ምናልባት ወንድሜን ከሞት የማትረፍ እድል ይኖረኝ ነበር። እሁድ ቀን ጠዋት ነው። ወደጓደኛዬ ኒካ ስነስርአት ለመሄድ ስነሳ ወንድሜ ቀድሞኝ ከቤት ወጥቶ ስለነበር ከቤታችን ደጃፍ የሚገኝ አስፋልት መንገድ ዳር ላይ ተቀምጦ አይቼው ነበር። ከአይኑ እስክጠፋ ቁጭ ባለበት ቦታ ሆኖ ያየኝ እንደነበር ያወቅኩት ርቄ ሄጄ ዘወር ስል ወደኔ አቅጣጫ ያይ እንደነበር በመታዘቤ ነው።

    ከሁለት ሰአታት በኋላ ፑል በመጫወት ላይ እንዳለ ተዝለፍልፎ ወደቀ ተብሎ ተደወለልኝ። ስደርስ ቤተዛታ ሆስፒታል ገብቶ ስትሬቸር ላይ ተኝቶ አገኘሁት። ሃኪሞች ከሻይ እስኪመለሱ እርዳታ አላገኘም። ቀስ በቀስ ራሱን ሙሉ በሙሉ ሳተ። ችግሩ ምን እንደሆነ አላወቅንም የነገረንም ሃኪም የለም። በመጨረሻ ቤተዛታ ከአቅሜ በላይ ነው አልችልም አለ ……ጥቁር አንበሳ በበኩሉ አልጋ የለኝም ሲል…እኛም ለጭንቅላት ምርመራ የታዘዘልንን ኤምአርአይ ፍለጋ ስንንከራተት ሰአቱ ገፋ። መጨረሻ ላይ ሀያት ሆስፒታል አልጋ ተገኝቶ የፅኑ ህሙማን ጥብቅ ክትትል ክፍል (ICU) ገባ። በዚያው ሁኔታ ሳለ በሶስተኛው ቀን ህይወቱ አለፈ።ገና በ22 አመቱ። ለቤታችን ታላቅ ሃዘን ሆነ። ዛሬ ድረስ ሁኔታውን ሳስበው እንባዬን ማቆም አልችልም። እጅግ የምወደውን ወንድሜን የነጠቀኝ ስትሮክ ነው።

    ከዚያ ጊዜ በኋላ የቅርብ ዘመዶቼን ጨምሮ የማውቃቸው ብዙ ሰዎች በስትሮክ ተጠቅተው አይቻለሁ። ብዙዎቹ ሞተዋል።ብዙዎቹ ፓራላይዝ ሆነዋል። በዚህ ሁለት ወር ብቻ የማውቃቸው ሶስት ሰዎች በስትሮክ ሞተዋል።

    በስእሉ ላይ እንደምትመለከቱት ስትሮክ ወደአንጎል የሚሄደው ደምስር በረጋ ደም በሚዘጋበት ጊዜ የደም ዝውውር ሲቋረጥ የሚከሰት የደም ወደአንጎል መፍሰስ የሚያስከትለው ከባድ የጤና አደጋ ነው። ከባድ የደም ግፊት፣ የልብና ኩላሊት በሽታ ለስትሮክ መከሰት ዋና ምክንያቶች መሆናቸውን ሃኪሞች ይናገራሉ።

    ብዙዎቻችን ስለማናስተውለው እንጂ የምንሰማው የዘመድ ወዳጆቻችን ድንገተኛ ሞትና ራስ መሳት ከስትሮክ ጋር ቁርኝት አለው። ይህ አደጋ ድንገት ባልታሰበ ሰአት ይከሰታል። ተኝተን፣ እየሰራን፣ እየበላን፣ እየተጫወትን፣ መንገድ ላይ ሆነን ሊከሰትብን ይችላል።

    በስትሮክ የተመታ ሰው ለብዙ ጉዳቶች ሊዳረግ ይችላል። አንዳንዶችን በሙሉ ወይም በከፊል ፓራላይዝ ያደርጋል። አንዳንዶቹን የአእምሮ ማስታወስ ችሎታቸውን በሙሉ ወይም በከፊል ይነጥቃቸውና ሚስትና ልጆቻቸውን ጭምር እንዲረሱ ያደርጋቸዋል። የከፋ ጊዜ ልክ ኮምፒውተር ፎርማት እንደሚደረገው ሁሉ ስትሮክ ያጠቃቸውን ሰዎችም አዕምሯቸው ምንም ሳያስቀር ሙሉ በሙሉ የመርሳት ችግር ይጋርጥባቸዋል። አንዳንዶቹ ላይ ደሞ ራስን ስቶ ሽንትና ሰገራ ለመቆጣጠር እስካለመቻል ምግብ እስካለመቀበልና በመጨረሻም እስከሞት ያደርሳቸዋል።

    የስትሮክ የከፋው ጠባይ የያዘውን ሰው አንዳንዴ ከሞቱት በላይ ከቆሙት በታች አድርጎ ማስቀረቱ ነው። እናት ለታመመ ልጇ ሞትን እስክትመኝ የታመመ ሰው በጠያቂ "አሁንስ በገላገለው " እስከሚባል ድረስ ተስፋ ያስቆርጣል።

    የጭንቅላት ቀዶ ሃኪሞች አንዳንዴ ከተሳካላቸው በአንጎል ውስጥ የፈሰሰ ደምን በመጥረግ ህይወት ያተርፋሉ ወይም ጉዳት ይቀንሳሉ። በኛ አገር ደረጃ በከባድ ስትሮክ ተመትቶ ሙሉ በሙሉ የመዳን ብቻ ሳይሆን ከሞት የመትረፍ እድል ራሱ አናሳ ነው። እግዚአብሄር ተጨማሪ የመኖር እድል የሰጠው ሰው ከሳምንታት ወይም ወራት ራስን መሳት በኋላ ሙሉ በሙሉ ተርፎ በተአምር ከሞት ወደህይወት ይመለሳል። የአንዳንዱን ህይወት ደግሞ እስከእድሜ መጨረሻው ድረስ አበላሽቶ ያስቀረዋል። በአጠቃላይ ስትሮክ መቼና እንዴት እንደሚከሰት ስለማይታወቅ ሰይጣን በሽታ በሉት። ሹክክ ብሎ መጥቶ ውድ ህይወታችንን ይነጥቀናል።ወይም ከነበርንበት ሙሉነት ወደከባድ ጎዶሎነት ይቀይረናል።

    ስትሮክን በተመለከተ ያለው መልካም ዜና አንድ ብቻ ነው። ምልክቱን አውቀን ከቀደምነው የሞት በትሩን የማስጣል እድል አለን ። በጣም ቀላል በሆኑ ዘዴዎች አንድ ሰው በስትሮክ ስለመመታቱ ማረጋገጥና በፍጥነት ወደሀኪም ወስደን ህይወቱን ማትረፍ እንችላለን። በርግጥ እግዜር ይጠብቅ ነው እንጂ በኛ ሃገር ሃኪሞችና ሆስፒታል ሁኔታ ብዙ ተስፋ ማድረግ አይቻል ይሆናል። ( በወንድሜ ሞት ያረጋገጥኩት ይህንኑ ነው)። ነገር ግን ባለሙያዎች እንደሚያረጋግጡት የስትሮክ ምልክት የታየበት ሰው በ3ሰአታት ጊዜ ውስጥ ሃኪም ጋር ከደረሰ ሙሉ በሙሉ ለመዳን እድል አለው። ዋናው ጥያቄ አንድ ሰው በስትሮክ ሲመታ የሚያሳያቸው ምልክቶች ምንድናቸው? እንዴትስ ማወቅ ይቻላል? የሚለው ነው።

    አንዳንድ ጊዜ ምልክቶቹን ለመለየት ከባድ ቢሆንም STROKE አንድን ሰው እንዳጠቃው ለማወቅ የምንረዳባቸውን ቀላል ዘዴዎች አሉ። ቀዳሚው ዘዴ የ STROKE ን የመጀመሪያዎቹን ሶስት ፊደላት በቃል ይዞ በአዕምሮ መመዝገብ ነው። STR

    S= smile. በትሮክ የተመታ ሰው ፈገግ ማለት ያዳግተዋል። ፊቱ ስሜት አልባ ይሆናል። አንድ ጊዜ ፈገግ እንዲል መጠየቅና ውጤቱን ማየት

    T =talk ስትሮክ አንደበት ስለሚይዝ የሚወጡ ቃላት እንዲንተባተቡና ትርጉመቢስ እንዲሆኑ ያደርጋል። ቀላል አረፍተነገርን ሳያቆራርጥ እንዲናገር መጠየቅ (ምሳሌ ቴሌቪዥኑን ስንት ትሸጠዋለህ? እንዲል )
    ውጤቱንም ማጤን

    R=raise hands ስትሮክ እጅና እግር እንዳይታዘዝ ያደርጋል። ሁለት እጆቹን ወደላይ እንዲያነሳ መጠየቅና ውጤቱን ማየት

    ከነዚህ አንዱን በትክክል መወጣት ከተሳነው የስትሮክ ምልክት ነውና ሃኪም ጋር በፍጥነት መውሰድ ጠቃሚ ይሆናል። በተጨማሪም ምላሱን ቀጥ አድርጎ እንዲያወጣ መጠየቅ ማውጣት ከተሳነው ወይም አጥፎና አጣሞ ካወጣው በስትሮክ የመመታት ምልክት ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል ።

    በቃ ይኸው ነው። ለሁሉም ሼር አድርገን ህይወት እናድን
    0 Comments 0 Shares