ባለፈው ቅዳሜ ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም ወደ ጠ/ሚኒስትርነት ሥልጣን ከመጡ ሦስት ወራት ያስቆጠሩትን ዶ/ርዐቢይ አህመድን ለመደገፍ በተዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የደረሰውን የቦንብ ጥቃት ለማጣራት፣ አሜሪካ፣ የኤፍቢአይባለሙያዎችን ወደ አዲስ አበባ እንደምትልክ አስታወቀች፡፡ከቦንብ ጥቃቱ ጋር በተያያዘ ከ30 በላይ ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው የተገለጸ ሲሆን እነዚህተጠርጣሪዎች በነገው ዕለት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሏል፡፡አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣን እንዳረጋገጡት፤ የአሜሪካ የፌደራል ምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ባለሙያዎችበአዲስ አበባ የደረሰውን የቦንብ ጥቃት ይመረምራሉ፡፡በዕለቱ ከደረሰው የቦንብ ጥቃት ጋር በተያያዘ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሣእንዲሁም የአዲስ አበባ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አስተባባሪ አቶ ተጋሩ ጎሃድባ ጨምሮ፣ ከ30 በላይተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ሆነው፣ ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡ባለፈው ቅዳሜ በመስቀል አደባባይ ጠ/ሚኒስትሩ ከተቀመጡበት መድረክ በግምት በ40 ሜትር ርቀት ላይ በፈነዳውቦንብ 165 ሰዎች ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ሁለቱ በህክምና ላይ እያሉ ህይወታቸው አልፏል፡፡ 15 ያህሉለከፍተኛ ጉዳት መዳረጋቸው የታወቀ ሲሆን ለአካል ጉዳት ከተዳረጉት መካከል በዲላ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድሆስፒታል ሃኪም የሆኑት ዶ/ር መኮንን ብርሃኑ በአደጋው አንድ እግራቸውን ማጣታቸውን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡አብዛኞቹ ተጎጂዎች እግራቸው፣ እጃቸውና ጭንቅላታቸው አካባቢ መጎዳታቸውን የህክምና ባለሙያዎች የገለጹ ሲሆን 3ሰዎች እግራቸው መቆረጡም ታውቋል፡፡ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጠ/ሚኒስትሩ በቦንብ ጥቃቱ ህይወታቸው ያለፈውን ሁለት ወጣት ቤተሰቦች በስልክአጽናንተዋል፡፡ በጥቃቱ ህይወታቸውን ያጡት የወላይታ ሶዶ ተወላጁ፣ የ28 ዓመቱ ወጣት ዮሴፍ አያሌው እናየምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ተወላጁ፣ የ25 ዓመቱ ጉሳ ጋዲሳ መሆናቸው ታውቋል፡፡የአዲስ አድማስ ዝግጅት ክፍል፤ በቦንብ ጥቃቱ ለደረሰው ሞትና የአካል ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘንእየገለጸ፣ለተጎጂ ቤተሰቦችና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል፡፡
ባለፈው ቅዳሜ ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም ወደ ጠ/ሚኒስትርነት ሥልጣን ከመጡ ሦስት ወራት ያስቆጠሩትን ዶ/ርዐቢይ አህመድን ለመደገፍ በተዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የደረሰውን የቦንብ ጥቃት ለማጣራት፣ አሜሪካ፣ የኤፍቢአይባለሙያዎችን ወደ አዲስ አበባ እንደምትልክ አስታወቀች፡፡ከቦንብ ጥቃቱ ጋር በተያያዘ ከ30 በላይ ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው የተገለጸ ሲሆን እነዚህተጠርጣሪዎች በነገው ዕለት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሏል፡፡አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣን እንዳረጋገጡት፤ የአሜሪካ የፌደራል ምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ባለሙያዎችበአዲስ አበባ የደረሰውን የቦንብ ጥቃት ይመረምራሉ፡፡በዕለቱ ከደረሰው የቦንብ ጥቃት ጋር በተያያዘ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሣእንዲሁም የአዲስ አበባ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አስተባባሪ አቶ ተጋሩ ጎሃድባ ጨምሮ፣ ከ30 በላይተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ሆነው፣ ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡ባለፈው ቅዳሜ በመስቀል አደባባይ ጠ/ሚኒስትሩ ከተቀመጡበት መድረክ በግምት በ40 ሜትር ርቀት ላይ በፈነዳውቦንብ 165 ሰዎች ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ሁለቱ በህክምና ላይ እያሉ ህይወታቸው አልፏል፡፡ 15 ያህሉለከፍተኛ ጉዳት መዳረጋቸው የታወቀ ሲሆን ለአካል ጉዳት ከተዳረጉት መካከል በዲላ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድሆስፒታል ሃኪም የሆኑት ዶ/ር መኮንን ብርሃኑ በአደጋው አንድ እግራቸውን ማጣታቸውን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡አብዛኞቹ ተጎጂዎች እግራቸው፣ እጃቸውና ጭንቅላታቸው አካባቢ መጎዳታቸውን የህክምና ባለሙያዎች የገለጹ ሲሆን 3ሰዎች እግራቸው መቆረጡም ታውቋል፡፡ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጠ/ሚኒስትሩ በቦንብ ጥቃቱ ህይወታቸው ያለፈውን ሁለት ወጣት ቤተሰቦች በስልክአጽናንተዋል፡፡ በጥቃቱ ህይወታቸውን ያጡት የወላይታ ሶዶ ተወላጁ፣ የ28 ዓመቱ ወጣት ዮሴፍ አያሌው እናየምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ተወላጁ፣ የ25 ዓመቱ ጉሳ ጋዲሳ መሆናቸው ታውቋል፡፡የአዲስ አድማስ ዝግጅት ክፍል፤ በቦንብ ጥቃቱ ለደረሰው ሞትና የአካል ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘንእየገለጸ፣ለተጎጂ ቤተሰቦችና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል፡፡
0 Comments
0 Shares