ሄዝቦላ ለፍንዳታው አጸፋ አመልሳለሁ ሲል ዛተ
“የሄዝቦላህ አባላት የሚጠቀሙባቸውን ኤሊክትሮኒክ የመልዕክት መቀባበያዎች (ፔጀሮች) ያፈነዳች እስራኤል ነች” ሲሉ ሄዝቦላህ እና የሊባኖስ መንግሥት ወንጅለዋታል። ትላንት ማክሰኞ በደረሱት ፍንዳታዎች ሁለት ህጻናትን ጨምሮ ቢያንስ አስራ ሁለት ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች ወደ 2800 የሚሆኑ ቆስለዋል፡፡ ሄዝቦላ የጋዛን የሃማስ ታጣቂዎች በመደገፍ ከእስራኤል ጋር መዋጋታችንን እንቀጥላለን ሲል ዛሬ ሐሙስ ተናግሯል፡፡ አክሎም “እስራኤል የሚደርስባትን ከባድ ቅጣት ትጠብቅ” በማለት...