ምዕራባዊያን አገሮች ኢራን ባለስልጣናት ላይ ማዕቀብ ጣሉ
ዩናይትድ ስቴትስ ካናዳ እና አውስትሬሊያ ዛሬ ረቡዕ በኢራን ባለስልጣናት ላይ ማዕቀብ ጥለዋል፡፡ ባለስልጣናቱ ማዕቀቡ የተጣለባቸው ከሁለት ዓመታት በፊት ሂጃቧን በተገቢው መንገድ አልተከናነበችም ተብላ በኢራን የሥነ ምግባር ፖሊስ ቁጥጥር ስር በዋለችበት ህይወቷ ካለፈው ከማህሳ አሚኒ ሞት ተከትሎ የተቃውሞ ሰልፎችን በማፈን እና ሰዎችን በማሰር ተሳትፈዋል ተብለው ነው፡፡
በዛሬው ማዕቀብ ተቃዋሚ ሰልፈኞችን በመግደል እና በማሰር እንዲሁም ጋዜጠኞችን በማሰር የተወነጀሉ...