በጎንደር ከተማ ትላንት በነበረው የተኩስ ልውውጥ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ ሦስት ሰዎች መቁሰላቸው ተነገረ
በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ትላንት ደርሷል በተባለው የተኩስ ልውውጥ በሁለት ቤተ እምነቶች ላይ በደረሰው ጥቃት 2 ሰዎች ሲሞቱ 3 ሰዎች መቁሰላቸውን በኢትዮጵያ የኦርቶዶህ ተዋህዶ የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ፡፡
ዋና ሥራ አስኪያጁ ሊቀ ህሩይ አባ ዮሴፍ ደስታ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት በከተማው ዙሪያ እና በከተማው ውስጥ በሚገኙ አማንኤል እና ፈለገህይወት ቤዛዊት ማርያም በተባሉ ቤተ ክርስቲያኖች አንድ አገልጋይና አንድ ተማሪ...