አሜሪካ ወታደሮቿን ሙሉ ለሙሉ ከኒጀር አስወጣች
አሜሪካ ወታደሮቿን ከኒጀር አስወጥታ ማጠናቀቋን አንድ ከፍተኛ የዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣን ትላንት ሰኞ አስታውቀዋል፡
የፔንታገን ቃል አቀባይ የሆኑት ሳብሪና ሲንግ፣ በኒጀር የሚገኘውን የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ለመጠበቅ ጥቂት ወታደሮች ብቻ መቅረታቸውንም ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
በአውሮፓዊያኑ 2024 መግቢያ ላይ፣ የኒጀር ወታደራዊ ጁንታ የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች በምዕራባዊቷ አፍሪካ ሃገር ያላቸውን ተልዕኮ የፈቀደውን ስምምነት እንዲያበቃ አድርጓል፡፡...