ጉባኤ ያካሄደው ህወሓት አቶ ጌታቸውን ጨምሮ 16 አመራሮችን ከፓርቲው ማባረሩን ገለፀ
በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የሚመራው ቡድን ባካሄደው ጉባኤ የተመረጠው አዲሱ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ 16 አመራሮቹን ከፓርቲው ማባረሩን እና ፖለቲካዊ ስራዎች እንዳይከውኑ ማገዱን አስታወቀ፡፡
በተጨማሪም በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ኃላፊነት ላይ ማስተካከያ እንዲደረግ እንደሚፈልግ ገልጿል።
ታግደዋል ከተባሉ አንዱ እና የክልሉ የኮምዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ሓላፊ አቶ ረዳኢ...