በሰሜን ጎንደር ግጭት ሰዎች መሞታቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት አስታወቁ
በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ በመንግስትና በፋኖ ቡድን ታጣቂዎች መካከል ትላንት በነበረው ግጭት ወደ ደባርቅ አጠቃላይ ሆስፒታል ቆስለው ከገቡት ውስጥ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ የሶስት አመት ህፃንን ጨምሮ 28 ሰዎች መቁሰላቸውን የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አስታውቀዋል፡፡
ስራ አስኪያጁ አቶ አለ አምላክ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ ሲናገሩ ከሟቾቹ ውስጥ አንድ ታጣቂና አንድ ሲቪል ናቸው ብለዋል ::ወደ ሆስፒታል ሳይደርሱ የህፃኑን አባት ጨምሮ ከ7 በላይ ስዎች መሞታቸውን...