• አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 26 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ትናንት ምሽት አንድ የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ ጨዋታን አስተናግዷል።

    በስታድ ሉዊዝ 2ኛ በዘንድሮው ቻምፒየንስ ሊግ በርካታ ጎሎቹን ያስቆጠረው ሞናኮ እና በጠንካራ የተከላካይ ክፍሉ ሁለት ግቦችን ብቻ ያስተናገደው የጣሊያኑ ጁቬንቱስ ተጫውተዋል።

    በጨዋታው የመጀመሪያ 20 ደቂቃዎች ሞናኮዎች ጥሩ የሚባሉ የጎል አጋጣሚዎችን ቢፈጥሩም ወጣቱ አጥቂ ኪሊያን ምባፔ የአንጋፋውን ግብ ጠባቂ ቡፎንን መረብ መድፈር አልቻለም።

    ከመስመር የተሻገሩለትን ኳሶች ወደ ጎል ቢሞክርም ትኩረት የማይለየው ጂያንሉጅ ቡፎን ጎል ከመሆን አድኗቸዋል።

    ቢያንኮኔሪዎቹ ከኔፕልስ ባዛወሩት አጥቂያቸው ጎንዛሎ ሄጉዌን የ28ኛ እና 58ኛ ደቂቃ ጎሎች ጨዋታውን 2 ለ 0 ማሸነፍ ችለዋል።

    ለጎሎቹ መቆጠር ከባርሴሎና በነጻ ዝውውር ያመጡት የቀኝ መስመር ተከላካዩ ዳኒ አልቬስ ትልቁን ሚና ተጫውቷል።

    አልቬስ ሄጉዌን ጎሎቹን እንዲያስቆጥር ኳሶቹን አመቻችቶ አቀብሎታል።

    ከጎሎቹ መቆጠር በኋላ ሞናኮዎች ተጭነው ለመጫዎት ቢሞክሩም ውጤቱን መቀልበስ ተስኗቸው ጨዋታው 2 ለ 0 ተጠናቋል።

    የመልሱ ጨዋታ በቀጣዩ ሳምንት ቱሪን ላይ ተደርጎ በደርሶ መልስ የሚያሸንፈው ቡድን ለዌልሱ የካርዲፍ ስታዲየም ፍጻሜ ትኬት ይቆርጣል።

    በምሽቱ የዩሮፓ ሊግ አንድ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታም ተደርጓል።

    በአምስተርዳም አሬና በተደረገው ጨዋታ የቀድሞው የአውሮፓ ሃያል አያክስ አምስተርዳም የፈረንሳዩን ኦሎምፒክ ሊዮንን 4 ለ 1 አሸንፎታል።

    ለአያክስ ከቼልሲ በውሰት የሄደው በርትራንድ ትራኦሬ፣ ካስፐር ዶልበርግ እና አሚን ዮንስ ጎሎቹን ሲያስቆጥሩ፥ ማቲው ቫልቡዬና ሊዮንን ከባዶ መሸነፍ ያዳነችውን ጎል ማስቆጠር ችሏል።

    የመልሱ ጨዋታ በቀጣዩ ሳምንት በፓርክ ኦሎምፒክ ሊዮን ተደርጎ የደርሶ መልሱ አሸናፊ ለፍሬንድስ አሬናው የፍጻሜ ጨዋታ ይቀርባል።

    ዛሬ ምሽት ደግሞ የእንግሊዙ ማንቼስተር ዩናይትድ ወደ ስፔን አምርቶ ከሴልታ ቪጎ ጋር ይጫወታል።

    አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ከሰሞኑ በተለየ ዛሬ ጠንካራ ቡድናቸውን ይዘው ወደ ሜዳ እንደሚገቡ ይጠበቃል።

    ለሳምንታት ከሜዳ ርቀው የቆዩት ተከላካዮቹ ክሪስ ስሞሊንግ እና ፊል ጆንስ ከቡድኑ ጋር ልምምድ የሰሩ ሲሆን፥ ምናልባትም በዛሬው ጨዋታ የመሰለፍ እድል ይኖራቸዋል ተብሏል።

    ከዚህ ባለፈም አማካዮቹ ፖል ፖግባ ሁዋን ማታም ከቡድኑ ጋር አብረው ልምምድ ሰርተዋል፤ በእሁዱ ጨዋታ ተጎድቶ የወጣው ተከላካዩ ኤሪክ ቤሊም ለዛሬው ጨዋታ ዝግጁ መሆኑን አሰልጣኙ ገልጸዋል።

    ከዚህ አንጻር ማንቼስተር ከሰሞኑ በተሻለ ጠንካራ ሆኖ ይቀርባል እየተባለ ነው።
    አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 26 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ትናንት ምሽት አንድ የግማሽ ፍጻሜ የመጀመሪያ ጨዋታን አስተናግዷል። በስታድ ሉዊዝ 2ኛ በዘንድሮው ቻምፒየንስ ሊግ በርካታ ጎሎቹን ያስቆጠረው ሞናኮ እና በጠንካራ የተከላካይ ክፍሉ ሁለት ግቦችን ብቻ ያስተናገደው የጣሊያኑ ጁቬንቱስ ተጫውተዋል። በጨዋታው የመጀመሪያ 20 ደቂቃዎች ሞናኮዎች ጥሩ የሚባሉ የጎል አጋጣሚዎችን ቢፈጥሩም ወጣቱ አጥቂ ኪሊያን ምባፔ የአንጋፋውን ግብ ጠባቂ ቡፎንን መረብ መድፈር አልቻለም። ከመስመር የተሻገሩለትን ኳሶች ወደ ጎል ቢሞክርም ትኩረት የማይለየው ጂያንሉጅ ቡፎን ጎል ከመሆን አድኗቸዋል። ቢያንኮኔሪዎቹ ከኔፕልስ ባዛወሩት አጥቂያቸው ጎንዛሎ ሄጉዌን የ28ኛ እና 58ኛ ደቂቃ ጎሎች ጨዋታውን 2 ለ 0 ማሸነፍ ችለዋል። ለጎሎቹ መቆጠር ከባርሴሎና በነጻ ዝውውር ያመጡት የቀኝ መስመር ተከላካዩ ዳኒ አልቬስ ትልቁን ሚና ተጫውቷል። አልቬስ ሄጉዌን ጎሎቹን እንዲያስቆጥር ኳሶቹን አመቻችቶ አቀብሎታል። ከጎሎቹ መቆጠር በኋላ ሞናኮዎች ተጭነው ለመጫዎት ቢሞክሩም ውጤቱን መቀልበስ ተስኗቸው ጨዋታው 2 ለ 0 ተጠናቋል። የመልሱ ጨዋታ በቀጣዩ ሳምንት ቱሪን ላይ ተደርጎ በደርሶ መልስ የሚያሸንፈው ቡድን ለዌልሱ የካርዲፍ ስታዲየም ፍጻሜ ትኬት ይቆርጣል። በምሽቱ የዩሮፓ ሊግ አንድ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታም ተደርጓል። በአምስተርዳም አሬና በተደረገው ጨዋታ የቀድሞው የአውሮፓ ሃያል አያክስ አምስተርዳም የፈረንሳዩን ኦሎምፒክ ሊዮንን 4 ለ 1 አሸንፎታል። ለአያክስ ከቼልሲ በውሰት የሄደው በርትራንድ ትራኦሬ፣ ካስፐር ዶልበርግ እና አሚን ዮንስ ጎሎቹን ሲያስቆጥሩ፥ ማቲው ቫልቡዬና ሊዮንን ከባዶ መሸነፍ ያዳነችውን ጎል ማስቆጠር ችሏል። የመልሱ ጨዋታ በቀጣዩ ሳምንት በፓርክ ኦሎምፒክ ሊዮን ተደርጎ የደርሶ መልሱ አሸናፊ ለፍሬንድስ አሬናው የፍጻሜ ጨዋታ ይቀርባል። ዛሬ ምሽት ደግሞ የእንግሊዙ ማንቼስተር ዩናይትድ ወደ ስፔን አምርቶ ከሴልታ ቪጎ ጋር ይጫወታል። አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ከሰሞኑ በተለየ ዛሬ ጠንካራ ቡድናቸውን ይዘው ወደ ሜዳ እንደሚገቡ ይጠበቃል። ለሳምንታት ከሜዳ ርቀው የቆዩት ተከላካዮቹ ክሪስ ስሞሊንግ እና ፊል ጆንስ ከቡድኑ ጋር ልምምድ የሰሩ ሲሆን፥ ምናልባትም በዛሬው ጨዋታ የመሰለፍ እድል ይኖራቸዋል ተብሏል። ከዚህ ባለፈም አማካዮቹ ፖል ፖግባ ሁዋን ማታም ከቡድኑ ጋር አብረው ልምምድ ሰርተዋል፤ በእሁዱ ጨዋታ ተጎድቶ የወጣው ተከላካዩ ኤሪክ ቤሊም ለዛሬው ጨዋታ ዝግጁ መሆኑን አሰልጣኙ ገልጸዋል። ከዚህ አንጻር ማንቼስተር ከሰሞኑ በተሻለ ጠንካራ ሆኖ ይቀርባል እየተባለ ነው።
    0 Comments 0 Shares
  • #ethiopia
    #ethiopia
    0 Comments 0 Shares
  • #ethiopia
    #ethiopia
    0 Comments 0 Shares
  • #ethiopia
    #ethiopia
    0 Comments 0 Shares
  • #ethiopia
    #ethiopia
    ALLAFRICA.COM
    Somalia: President Farmajo Cuts Short Ethiopia Visit
    President of Somalia, Mohamed Abdullahi Mohamed Farmajo, on Wednesday, said he was cutting an official visit to neighbouring Ethiopia in order to return and participate in the burial of the youngest minister in his government.
    0 Comments 0 Shares
  • KEFI Minerals inks Tulu Kapi agreement with Ethiopia government
    KEFI Minerals said subsidiary KEFI Minerals (Ethiopia) Ltd (KME) and the Federal Democratic Republic of Ethiopia have signed the shareholders' agreement for the incorporation, ownership and operation of Tulu Kapi Gold Mines Share Company Ltd (TKM).
    0 Comments 0 Shares
  • WWW.GOOGLE.COM
    Ethiopia: Refugee Influx Into Ethiopia - Challenges & Solutions
    Opinion - The IGAD region hosts 2.46 million refugees, while also producing 3.12 million refugees. Ethiopia shelters 33 percent of the total number of refugees in the IGAD region and 2.3 percent of the total number of refugees world-wide, while producing 0.5 percent of the world's total number of refugees, thus caring for more than its share of the global refugee burdens. The list also includes 20,000 refugees residing in Addis Ababa for reasons related to special medical attention, humanitarian issues and serious p
    0 Comments 0 Shares
  • አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 26 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በአለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) ወርሃዊ የሀገራት ደረጃ ኢትዮጵያ በነበረችበት 124ኛ ላይ ተቀመጠች።

    ወርሃዊው የፊፋ የሀገራት የእግር ኳስ ደረጃ ይፋ ሆኗል።

    ኢትዮጵያ ባላፈው ወር 20 ደረጃዎችን ማሽቆልቆሏ የሚታወስ ነው፡፡

    ፊፋ ባወጣው የወሩ ደረጃም ብራዚል፣ አርጀንቲና እና ጀርመን ካለፈው ወር የደረጃ ለውጥ ሳያደርጉ ባሉበት በቅደም ተከተል ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡

    ከአፍሪካ ግብፅ ቀዳሚ ስትሆን ሴኔጋል እና የወቅቱ የአፍሪካ ሻምፒዮን ካሜሩን ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል።

    የአፍካ መሪዎቹ ሀገራት ከዓለም በደረጃቸው ቅደም ተከተል መሰረት 19ኛ፣ 30ኛ፣ 33ኛ ላይ ይገኛሉ፡፡

    በወሩ ማላዊ 14 ደረጃዎችን በማሽቆልቆል ቀዳሚዋ ስትሆን 114ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡

    ከፍተኛ የደረጃ ማሻሻል ያሳዩ ሀገራት ደግሞ ማዳጋስካር 9 ደረጃዎችን በማሻሻል 111ኛ፣ ደቡብ ሱዳን 7 ደረጃዎችን በማሻሻል 146ኛ ደረጃን መያዛቸው በመረጃው ተጠቅሷል።

    በደረጃው ግርጌ ላይ ደግሞ አንጉይላ፣ ባህማስ፣ ኤርትራ፣ ጂብራልተር፣ ሶማሊያ እና ቶንጋ ያለምንም ነጥብ 206ኛ ደረጃ ላይ መቀመጣቸውን ከፊፋ ድረ ገጽ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
    አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 26 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በአለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) ወርሃዊ የሀገራት ደረጃ ኢትዮጵያ በነበረችበት 124ኛ ላይ ተቀመጠች። ወርሃዊው የፊፋ የሀገራት የእግር ኳስ ደረጃ ይፋ ሆኗል። ኢትዮጵያ ባላፈው ወር 20 ደረጃዎችን ማሽቆልቆሏ የሚታወስ ነው፡፡ ፊፋ ባወጣው የወሩ ደረጃም ብራዚል፣ አርጀንቲና እና ጀርመን ካለፈው ወር የደረጃ ለውጥ ሳያደርጉ ባሉበት በቅደም ተከተል ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ ከአፍሪካ ግብፅ ቀዳሚ ስትሆን ሴኔጋል እና የወቅቱ የአፍሪካ ሻምፒዮን ካሜሩን ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል። የአፍካ መሪዎቹ ሀገራት ከዓለም በደረጃቸው ቅደም ተከተል መሰረት 19ኛ፣ 30ኛ፣ 33ኛ ላይ ይገኛሉ፡፡ በወሩ ማላዊ 14 ደረጃዎችን በማሽቆልቆል ቀዳሚዋ ስትሆን 114ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ ከፍተኛ የደረጃ ማሻሻል ያሳዩ ሀገራት ደግሞ ማዳጋስካር 9 ደረጃዎችን በማሻሻል 111ኛ፣ ደቡብ ሱዳን 7 ደረጃዎችን በማሻሻል 146ኛ ደረጃን መያዛቸው በመረጃው ተጠቅሷል። በደረጃው ግርጌ ላይ ደግሞ አንጉይላ፣ ባህማስ፣ ኤርትራ፣ ጂብራልተር፣ ሶማሊያ እና ቶንጋ ያለምንም ነጥብ 206ኛ ደረጃ ላይ መቀመጣቸውን ከፊፋ ድረ ገጽ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
    0 Comments 0 Shares